PODCAST · news
እንወያይ | Deutsche Welle
by DW
ኢትዮጵያን በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ ከተለያዩ እንግዶች እና በተለያዩት የዓለም ሀገሮች ከሚገኙት ወኪሎቻችን ጋ የምናካሂደውን እና በየሣምንቱ እሁድ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከአሥር ደቂቃ ላይ የሚተላለፈውን የውይይት ዝግጅት ያዳምጡ።
-
50
የሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ዝግጅትና ተግዳሮቶቹ
ከ20 በላይ ሀገራዊ እና ከ40 በላይ ክልላዊ ፓርቲዎች ይሳተፉበታል የተባለው ሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ሊካሄድ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የአንድ ወር ጊዜ ነው የቀረው። ቦርዱ በስድስት ክልሎች «የፀጥታ እና አስቻይ የፖለቲካ ምህዳር»ን እንዲገመግም ያደራጀውን ቡድን ማሰማራቱን ባለፈው ሳምንት አስታውቋል።
-
49
የእሥራኤል-ዩናይትድ ስቴትስ ኢራን ጦርነት ዳፋ ለኢትዮጵያ፦ እንወያይ
የእሥራኤል-ዩናይትድ ስቴትስ ኢራን ጦርነት የተኩስ አቁሙ ቢራዘምምም በሆርሙዝ ሰርጥ ኢራን ቁጥጥሯን በማጥበቋ እና ዩናይትድ ስቴትስም በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችው ገደብ ባለመነሳቱ ውጥረቱ አይሎ ቀጥሏል ። ለመሆኑ ይህ የመካከለኛው ምሥራቅ ውጥረት መቀጠሉ ኢትዮጵያ ላይ ያሳደረው ጫና እንዴት ይቃኛል? ሙሉውን ውይይት ያድምጡ ።
-
48
ውይይት፤ ኢትዮጵያ ብርቱ ፈተና የደቀነውን የነዳጅ እጥረት እንዴት ትወጣ?
የኢራን ጦርነት በዓለም አቀፍ የነዳጅ አቅርቦት ሰንሰለት ላይ የፈጠረው መስተጓጎል ለመቋቋም ሕዝቡ እና ተቋማት በከፍተኛ ጥንቃቄ ነዳጅ እንዲጠቀሙ ቀደም ሲል የኢትዮጵያ መንግስት አስጠንቅቋል። የነዳጅ ግብይትም መንግስት ባስቀመጠው ታሪፍ መሰረት እንዲከናወን አሳስቧል። ያም ሆኖ ችግሩ ከዓቅም በላይ መሆኑን ነዋሪዎች እየገለጹ ነው።
-
47
እንወያይ፤ የጦርነቱ ዳፋ ወደኛ እንዳይደፋ
ከኢኮኖሚ አንጻር የሖርሙዝ ሠርጥ በዓለም ገበያ ከሚሸጠው የአፈር ማዳበሪያ እስከ 30 በመቶ ወይም 16 ሚሊዮን ቶን የሚጓጓዝበት እንደሆነ ይታወቃል። የአለማችን 20 % የነዳጅ ግብይትም በዚሁ መስመር ይተላለፋል።
-
46
እንወያይ፤የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ፍጥጫ ወደየት ያመራ ይሆን?መፍትሄውስ ምን ይሁን?
በ2010 ዓ/ም እንደገና የጀመረው የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ግንኙነት፤ በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ አድናቆት የተቸረው እና የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትርን የሰላም ኖቬል እስከማሸለም የደረሰ ነበር።ይሁንና የሀገራቱ ሰላማዊ ግንኙነት የዘለቀው ለጥቂት ዓመታት ሲሆን፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ አለመግባቱ እየተካረረ መጥቷል።
-
45
የትግራይ ግጭት እና ዘላቂው መፍትሔ
የፌደራል ኃይሎች ከአወዛጋቢዎቹ ከአላማጣ እና ኮረም እንዲሁም ከሌሎች አጎራባች ከተሞች መውጣታቸው ከተሰማ በኋላ ነዋሪዎች ጦርነት ይቀሰቀሳል በሚል ከከተሞቹ መሸሽ መጀመራቸው ሌላው ስጋቱ እንዲጨምር ያደረገ ክስተት ነበር። በትግራይ የድሮን ጥቃቶች በሁለት አካባቢዎች ተፈጸሙ የመባሉ ዜና በሀገር ውስጥም በውጭም ጉዳዩን ይበልጥ አሳሳቢ አድርጎታል።
-
44
ውይይት፤ የትራምፕ ሽምግልና ለኢትዮጵያ ምን ይዞ ይመጣ ይሆን?እንዴትስ ጥቅሟን ታስከብር?
የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ የአባይ ውሃ ባለድርሻነት ለዘለቄታው እልባት እንዲያገኝ በሚል፤iኢትዮጵያ እና ግብፅጽን ዳግም ወደ ድርድር ለማምጣት ሀገራቸው ቁርጠኛ መሆኗን ደጋግመው ገልፀዋል.።ያም ሆኖ ትራምፕ በተለያዩ ጊዜዎች የሚሰጧቸው ወደ ግብፅ ያዘነበሉ አስተያየቶች የገለልተኝነት እና የፍትሃዊነት ጥያቄ ማስነሳቱ አልቀረም።
-
43
ባለሙያዎች ከዓመታት በኋላ ወደ ነጠላ አሐዝ ስለወረደው የኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት ምን ይላሉ?
የዋጋ ግሽበት ከዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ነጠላ አሐዝ ዝቅ እንዳለ የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት አስታውቋል። የዋጋ ግሽበት በታኅሳስ ወደ 9.7% ዝቅ እንዳለ የተገለጸው ሸማቾች በኑሮ ውድነት በሚፈተኑበት ወቅት ነው። ለመሆኑ የብሔራዊ ባንክ ገዥ “እጅግ የሚያስደምም” ያሉት ነጠላ አሐዝ የዋጋ ግሽበት በባለሙያዎች እንዴት ይታያል?
-
42
እንወያይ፦ ዓለም በጎርጎሪዮሱ 2025 ዓ.ም
የጎርጎሪዮሱ 2025 ዓ.ም ተጠናቅቆ አዲስ ዓመት ከባተ እነሆ ዛሬ አራተኛ ቀኑ ተቆጥሯል ። የዛሬው እንወያይ የጎርጎሪዮሱ 2025 ዐበይት ክስተቶችን ወደ ኋላ መለስ ብሎ ይቃኛል ። በዛሬው እንወያይ መሰናዶ ሦስት ተሳታፊዎች ትንታኔ ሰጥተዋል ።
-
41
ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ስደተኞች በአሜሪካና በአውሮፓ የገጠማቸው ፈተና
ከ5ሺህ በላይ ይሆናሉ የተባሉ ኢትዮጵያውያን ድንገት ወደሀገራቸው እንዲሚመለሱ ተነግሯቸዋል። ኢትዮጵያውንንም ተጠቃሚ ያደርግ የነበረው ቋሚ የመኖሪያና የስራ ፈቃድ የሚያስገኘው የDV መርሃ-ግብር መቋረጡ ተነግሯል። እነዚህ ስደተኞችን የሚያዋክቡ አሰራሮች ወደ አውሮጳ ኅብረት አባል ሀገራትና ብሪታንያም ጭምር የመዛመታቸው አዝማሚያ ያሰጋል።
-
40
የመገናኛ ብዙኀን ሁኔታና መጪው ምርጫ በኢትዮጵያ
ከጥቂት ዓመታት በፊት የዓለም የፕረስ ነጻነትን ቀን የማስተናገድ እጋጣሚ ሰምሮላት በነበረው ኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኀን የነጻነት ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ መምጣቱ መነገር ከጀመረ ውሎ አደረ።
-
39
እንወያይ፤ ጦርነት ያባባሰው ወሲባዊ ጥቃት በአማራ ክልል
ጾታን መሰረት ያደረገ ጥቃት በኢትዮጵያ ስር የሰደደ ችግር ቢሆንም፣ በአገሪቱ እየተከሰቱ ባሉ የትጥቅ ግጭቶች ሳቢያ ጥቃቱ እየተባባሰ መምጣቱ ይነገራል። በአማራ ክልል ላለፉት ሁለት አመታት በፌደራል መንግስትና በፋኖ ሃይሎች መካከል እየተካሄደ ያለው ግጭትም በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ወሲባዊ ጥቃት ማባባሱን የቅርብ ጊዜ ዘገባዎች ያመለክታሉ።
-
38
ውይይት፦ ምን ያስተሳስረው ይሆን? ግጭት ኢትዮጵያ እና ጎረቤት አገራት
ውይይት፦ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚከሰተው ግጭት ሱዳን ውስጥ፥ የሱዳኑ ኢትዮጵያ ውስጥ ነጸብራቁ በጉልኅ ይታያል ። ከፍ ሲል ግብጽ ከወደታች ደግሞ ሶማሊያም በግጭት ውጥረቱ ስማቸው በተደጋጋሚ ይነሳል ። የኢትዮጵያ መንግሥትን ደግፎ በትግራይ ክልል ጦር ያዘመተው የኤርትራ መንግሥት ያኔ ከደገፈው ጋር አሁን ዐይን እና ናጫ ከመሆንም አልፈው ተፋጥጠዋል ።
-
37
ያንዣበበው የጦርነት ስጋት እንዲገታ ...
የኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥትና ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ፕሪቶሪያ-ደቡብ አፍሪቃ ላይ ግጭትን የማቆም ስምምነት ከተፈራረሙ ባለፈዉ ጥቅምት 23 ሶስኛ ዓመቱን አስቆጥሯል። ሶስቱ ዓመታቱ ብዙዎች እንደሚሉት ሁለቱ ኃይላት በስምምነታቸው መሰረት ግዴታቸውን ያልተወጡበት ወይም ሊወጡ ያልፈለጉበት ሰላምም ግጭት ያልነበረበት ሆኖ ነው ያለፈው።
-
36
የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ ገበያ እና ብር ወዴት እያመሩ ነው?
የውጭ ምንዛሪ ግብይት በአቅርቦት እና ፍላጎት እንዲወሰን ከተደረገ ወዲህ ኢትዮጵያ ከሸቀጦች የወጪ ንግድ የምታገኘው ገቢ ዕድገት ቢያሳይም ብር እየተዳከመ ነው። የወርቅ ኤክስፖርት መሻሻል ብር እንዲረጋጋ ሊያደርግ እንደሚችል ብሔራዊ ባንክ ተስፋ አድርጓል። ሦስት ባለሙያዎች የተሳተፉበት ውይይት የምንዛሪ ገበያው ብር ላይ ያሳደረውን ተጽዕኖ ይፈትሻል።
-
35
መፍትሄ ያጣው ግጭትና የልማት እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ
መንግሥት የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን እያከናወነ መሆኑን ይገልጻል። በቅርቡም የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ምረቃ እና አዳዲስ እንቅስቃሴዎችም ታይተዋል። የሀገሪቱ ኤኮኖሚዊ እድገትን ከማፋጠን በተጨማሪ የኅብረተሰቡን ኑሮውን ሊያሻሽሉ እንደሚችሉም ተስፋ ይሰጣል።
-
34
እንወያይ፤ መንግሥት ለሕዝብ ጥያቄዎች ከምርጫ በፊት መልስ ያገኝላቸዉ ይሆን?
የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሥራ ሊጠናቀቅ የቀረዉ ሦስት ወራት ገደማ ነዉ። ኮሚሽኑ ከህዝብ ያሰባሰባቸዉን ጥያቄዎችና አጀንዳዎች ለመንግሥት ያቀርባል።በሌላ በኩል በያዝነዉ 2018 ዓመት ብሔራዊ ምርጫ መካሄድ ይኖርበታል። ይሁንና መንግሥት ከህዝብ ለተሰበሰቡት አጀንዳዎች ከምርጫ መፊት መልስ ለመስጠት ጊዜና አቅም ይኖረዉ ይሆን?
-
33
አሳሳቢው መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት በኢትዮጵያ
በኢትዮጵያ መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት እና በሰዎች የመነገድ ወንጄል ሰፊ እና ውስብስብ ችግር መሆኑን በዘርፉ የሚሰሩ ዓለም አቀፍ እና ሀገር በቀል ተቋማት ይገልፃሉ።ይህ ችግርም በተለይም ወጣቶችን ሰለባ እያደረገ ሲሆን ፤አንድ ገለልተኛ ዘገባ እንዳመከተው በጅቡቲ በኩል በአማካይ 12,000 ኢትዮጵያውያን በየወሩ ወደ ሳውዲ አረቢያ ይጓዛሉ።
-
32
አንድ - ለ - አንድ:- ከኡስታዝ ጀማል በሽር ጋር
ኡስታዝ ጀማል በሽር በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ የህዳሴ ግድብ የግንባታ ሂደቱን በማጠልሸት ቅቡልነት ለማግኘት ግብጾች የተቀናጀ የሚዲያ ዘመቻ እያካሄዱ መሆኑን አይቼ ቁጭት ይዞኝ እኔም የዛሬ ስድስት ዓመት ስለ ሕዳሴ ግድብ ስለ አባይ ዉኃ አጠቃቀም፤ የኢትዮጵያን አቋም ይዤ ለግብፅና የአረቡን ሚዲያ መሞገት ጀመርኩ ብለናል።
-
31
የመስከረም 11 ቀን 2017 ዓ.ም እንወያይ፤ «የጦርነት ዳመና»
ህወሐት በአለፈው እሁድ ባሰራጨው መግለጫ ደግሞ የኢትዮጵያ መንግስትን የፕሪቶርያ ውል በመጣስ በትግራይ ግጭት ለመፍጠር በአፋር እና በምዕራብ ትግራይ ታጣቂዎች እየመለመለ እና እያስታጠቀ ነው ሲል ከሷል።
We're indexing this podcast's transcripts for the first time — this can take a minute or two. We'll show results as soon as they're ready.
No matches for "" in this podcast's transcripts.
No topics indexed yet for this podcast.
Loading reviews...
Loading similar podcasts...