EPISODE · Mar 24, 2026 · 1H
ካሳ እና ፍትህ፡ በፓን አፍሪካዊ ማህደረ ትውስታ እና በዓለም አቀፍ የኃይል ፖለቲካ መካከል
from Drum of Changes
“አፍሪካ የራሷን ታሪክ፣ የራሷን እውነታ ለዓለም የምትነግርበት ድምፅ ይኖራት ዘንድ ፍፁም አስፈላጊ ነው። ምክኛቱ ደግሞ እስከዛሬ ድረስ አፍሪካን ብሎም የአፍሪካን ታሪክ በራሳቸው መንገድ ሲተርኩ ስለአፍሪካ ሲናገሩ የቆዩት አውሮፓውያን ናቸውና። ከአፍሪካ ውጭ [በአሜሪካ] እንዳደገች አንዲት ጥቁር ሰው እውነቱን ለመናገር ስለአፍሪካ መልካም ነገር ሰምቼ አላውቅም” ሲሉ ፓናፍሪካኒስቷ ጃኔል ሆይሌት ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ ዝግጅታችን የባሪያ ንግድ፣ የቅኝ ግዛት እና መዋቅራዊ ብዝበዛ በጥቁር ሕዝቦች ላይ ጥሎ ስላለፈው አሻራ እንቃኛለን። ጨምረንም መላው የጥቁር ሕዝቦች ለፍትህ እና ካሳ የሚያደርጉትን የትግል ጉዞ እንመለከታለን። በዚህ ጉዞ ውስጥም ለጥቁር ሕዝቦች የቆሙ ተቋሟት ዛሬም ድረስ ከቀጠለው የቀድሞ ቅኝ ገዥዎች ግብዝነት ጋር የሚያደርጉትን ትግል እንፈትሻለን። ለዚህም ታዲያ ኑሯቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉት ጥቁር አሜሪካዊቷ ፓናፍሪካኒስት፣ ደራሲ እና ወደ አፍሪካ የመመለስ ንቅናቄ አንቂ ጃኔል ሆይሌትን ጋብዝን በእነዚህ ጉዳዮች ዙሪያ ሐሳባቸውን አጋርተዉናል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራሙን ያዳምጡ:
NOW PLAYING
ካሳ እና ፍትህ፡ በፓን አፍሪካዊ ማህደረ ትውስታ እና በዓለም አቀፍ የኃይል ፖለቲካ መካከል
No transcript for this episode yet
Similar Episodes
Mar 26, 2026 ·1m
Mar 19, 2026 ·34m
Feb 18, 2026 ·11m
Feb 11, 2026 ·45m