አፍሪካ፡ በባለ ብዙ ወገን ዓለም ውስጥ እያደገ ያለ አህጉር episode artwork

EPISODE · Dec 23, 2025 · 1H

አፍሪካ፡ በባለ ብዙ ወገን ዓለም ውስጥ እያደገ ያለ አህጉር

from Sovereignty Sources

የአፍሪካ ሩሲያ ግንኙነት የእኩልነት መርህን መሰረት ያደርገ ነው '' ሉዓላዊ ትብብር የአፍሪካን ሉዓላዊነት እንደሚያመጣ ማየት ትችላላችሁ። ይህ የጌታና አሽከር ወይም የፈረስና ጋላቢ ግንኙነት አይደለም። የጋራ እሴቶች ባላቸው ህዝቦች መካከል ያለ ግንኙነት ነው። እነዚህ የጋራ እሴቶች ሉዓላዊ አፍሪካን ለመፍጠር እንዲሁም ሉዓላዊ የሩሲያ ፌዴሬሽንን ለማበረታታት የምንጠቀምባቸው ናቸው'' ሲሉ የዙምባቡዌ የውጭ ግንኙነትና ዓለምአቀፍ ንግድ ሚኒስትር ፕሮፌሰር አሞን ሙሩዊራ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።ሶስት አንኳር ጉዳዮችን በምንዳስስበት የዛሬው ፕሮግራማችን በክፍል አንድ አፍሪካ በባለ ብዙ ወገን ዓለም ያላት ሚናን የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እ.ኤ.አ ታህሳስ 19፣ 2025 ባደረጉት የዓመቱ ማጠቃለያ ንግግር ስለአፍሪካ ካነሷቸው ሀሳቦች ጋር በማጣመር በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የፖሊሲ ጥናቶች ረዳት ፕሮፌሰሩ ሙከረም ሚፍታህ (ዶ/ር) ጋር እንወያያለን። በሁለተኛው ክፍል ደግሞ ከታህሳስ 19 - 20፣ 2025 በካይሮ፣ ግብፅ የተደረገውን 2ኛው የሩሲያ - አፍሪካ የሚኒስትሮች ጉባዔን የደቡብ ሱዳን የዉጭ ግንኙነትና ዓለምአቀፍ ትብብር ሚኒስትር መንዴይ ሲማያ ኩምባ እና የዛምቢያ የዉጭ ግንኙነትና ዓለማአቀፍ ትብብር ሚኒስትር ሙላምቦ ሄምቤን አነጋግረናቸዋል። ፀረ - ቅኝ ግዛትና ተያያዥ ጉዳዮችን ከዓለም የፖለቲካና ፍልስፍና ተንታኙ ጋብርዔል አሱኮ ጋር በሶስተኛው ክፍል ቃኝተነዋል። ''የአፍሪካ ሀገራት በምጣኔ ሐብት ዕድገት፣ ሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች መሻሻል እያሳዩ ነው። ሉዓላዊነት አስፈላጊ ነገር ነው — እንደ ራሲያ እና ቻይና ያሉ ሀገራት ብሪክስም እየጎለበተ መምጣታቱ ባለአንድ ወገኑን ዓለም የመታደስ ግዴታ ውስጥ እያስገባው ነው ''ሲሉ በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የፖሊሲ ጥናቶች ረዳት ፕሮፌሰሩ ሙከረም ሚፍታህ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን  ያዳምጡ:

Episode metadata supplied by the publisher feed · Published Dec 23, 2025

Embed this episode

NOW PLAYING

አፍሪካ፡ በባለ ብዙ ወገን ዓለም ውስጥ እያደገ ያለ አህጉር

0:00 1:00:00

No transcript for this episode yet

We transcribe on demand. Request one and we'll notify you when it's ready — usually under 10 minutes.

No similar episodes found.

Frequently Asked Questions

How long is this episode of Sovereignty Sources?

This episode is 1 hour and 0 minutes long.

When was this Sovereignty Sources episode published?

This episode was published on December 23, 2025.

Can I download this Sovereignty Sources episode?

Yes. Use the download control on the episode player to save the publisher-provided media file.
URL copied to clipboard!