EPISODE · May 28, 2026 · 10 MIN
DW Amharic የግንቦት 20 ቀን 2018 የዓለም ዜና
from የዓለም ዜና · host DW
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ በጥሞና ወቅት “ፕሮጀክት ማስጀመር እና ማስመረቅ” ከለከለ። ክልከላው የምርጫውን ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ያግዛል በተባለው የጥሞና ጊዜ ከማይደረጉ እንቅስቃሴዎች ውስጥ የተካተተ ነው። ከኢትዮጵያ መንግሥት የሚዋጋው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ከነገ ጀምሮ በአማራ ክልል “ለተከታታይ አምስት ቀናት ከአንቡላንሶች በስተቀር ሁሉም መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ መደረጋቸውን” አስታወቀ። የኢትዮጵያ መንግሥት አገሪቱ አንድ ቢሊዮን ዶላር የተበደረችበት ቦንድ ባለቤቶችን ከሚወክል ጊዜያዊ ኮሚቴ ጋር ያደረገው ውይይት ውጤታማ ሳይሆን መቅረቱን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።
NOW PLAYING
DW Amharic የግንቦት 20 ቀን 2018 የዓለም ዜና
No transcript for this episode yet
Similar Episodes
May 13, 2026 ·18m
May 12, 2026 ·21m
May 11, 2026 ·13m
May 11, 2026 ·19m
May 8, 2026 ·27m
May 7, 2026 ·25m