PODCAST · news
የዓለም ዜና
by DW
ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ ማድመጥ ትችላላችሁ። የዶይቼ ቬለ ዜና በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በየዕለቱ በቀጥታ ይደመጣል።
-
100
የሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
የተመድ የኢቦላ ወረርሽኝ አፍሪቃን እስከ 3,6 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ያስወጣታል አለ። የኬንያ ፖሊስ በዛሬው ዕለት እገታን በመቃወም አደባባይ የወጡ ናቸው በተባሉ ሰዎች ላይ ጥይት ተኩሶ አንድ ሰው መግለደሉን እማኞች አመለከቱ። ሁለት ሰዎችም በጥይት ተጎድተዋል። የተመድ የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት በሱዳን አል ኦቢድ ጉዳይ አስቸኳይ ክርክር ሊያካሂድ መሆኑ ተገለጸ። በተጠቀሰችው ከተማ ዙሪያ የፈጥኖ ደራሹና ደጋፊዎቹ ኃይሎች መከማቸታቸው ስጋት አስከትሏል። ኢራን ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በመጪዎቹ ቀናት የመገናኘት እቅድ የለኝም አለች። ሁለት የአሜሪካ ልዑካን በኢራን ጉዳይ ለመነጋገር ዛሬ ቀጠር መግባታቸው ተዘግቧል።
-
99
DW Amharic የሰኔ 22 ቀን 2018 የዓለም ዜና
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የሶማሊያ ፕሬዝደንት ሐሰን ሼክ ማሕሙድ ተገናኙ። ለ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና የሚቀመጡ ተማሪዎች ሞባይል ስልክ፣ ቅንጡ የእጅ ሰዓቶችና ማዳመጫዎች ወደ መፈተኛ ክፍል ይዘው መግባት ተከለከሉ። ኢትዮጵያ አንድ ቢሊዮን ዶላር የተበደረችበት ቦንድ ባለቤቶችን ከሚወክል ጊዜያዊ ኮሚቴ ጋር የዕዳ አከፋፈል ሽግሽግ ለማድረግ በመርኅ ደረጃ ከሥምምነት መደረሱን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ። የኬንያ መንግሥት ከአሜሪካ ጋር ሊፈራረም ነው የተባለው የውድ ማዕድናት ፍለጋ “ግልጽነት ይጎድለዋል” የሚል ክስ በፍርድ ቤት ቀረበበት። በጀርመን ኒደር ዛክሰን ግዛት ሽታደ ከተማ በተከፈተ ተኩስ 5 ሰዎች ተገደሉ
-
98
የዕሁድ ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ. ም ፤ የዓለም ዜና
የዛሬው የዓለም ዜና በሳውዲ አረቢያ እና በፈረንሳይ በደረሰ የሄሊኮፕተር እና የአውሮፕላን አደጋ 25 ሰዎች መሞታቸውን፣ በአውሮጳ በተከሰተው ከፍተኛ የሙቀት ማዕበል በአንድ ሳምንት ብቻ ከ1,300 በላይ ሞት መመዝገቡን፣ ቢያንስ 191 ሚሊዮን ሰዎች ለ35 ዲግሪ ሴልሺየስ ሙቀት ይጋለጣሉ መባሉን፣ ኢራን የአሜሪካን ጥቃት ተከትሎ በባህሬን እና ኩዌት ላይ ጥቃት ማድረሷን እንዲሁም የዩክሬንን ጥቃት ተከትሎ የሩሲያው መሪ የሀገራቸውን ደህንነት ለማረጋገጥ ቃል መግባታቸውን አካቷል።
-
97
የሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና
• በኢትዮጵያ የሚገኘው የአውሮጳ ኅብረት ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) እያካሔደ ነው የተባለው አስገዳጅ ወታደራዊ ምልመላ የፕሪቶሪያ ግጭት የማቆም ስምምነት በግልጽ የጣሰ ነው ሲል ነቀፈ። • በሱዳን ኤል-ኦቤይድ ከተማ የሚካሄደው ውጊያ ወደ ከፋ ደረጃ ላይ ሊደርስ ይችላል ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስጠነቀቀ። • የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መንግሥት በጎረቤት ሩዋንዳ ላይ በዓለም አቀፉ የወንጀል መዳኛ ፍርድ ቤት (ICJ) ክስ መሰረተች። • ኢራን አሜሪካን "ጦርነቱን ለማቆም የተደረገውን ስምምነት ጥሳለች" ስትል ከሰሰች።
-
96
የዓርብ ሰኔ 19 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
መቐለ፥ ሕወሓት ለሒውማን ራይትስ ዎች ምላሽ ሰጠ፤ ካርቱም፥ በሱዳን ኤል ኦቤይድ ከተማ ላይ ሌላ ፍጅት እንዳይከሰት አሥግቷል፤ ቱኒስ፥ ኃዋቂዋ ቱኒዚያዊት የ75 ዓመት የመብት ተሟጋች 25 ዓመት እስር ተፈረደባቸው፤ ዋሽንግተን፥ የዩናይትድ ስቴትስ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሔይቲ እና ሶሪያ ዜጎች በገፍ ከአገር እንዲባረሩ የሚያስችል መንገድ ጠረገ፤ ፓሪስ፥ አውሮጳን የመታው የሙቀት ማእበል እንደበረታ ነው፤ ካራካስ፥ ከብርቱው ርእደ መሬት የተረፉትን ለማዳን ርብርቡ ቀጥሏል፤ ኒው ጄርዚ፥ የዓለም ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ እየተገባደደ ነው
-
95
የሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
የኬንያ ፖሊስ በዛሬው ዕለት ናይሮቢ በሚገኘው ዋና የፖሊስ ጣቢያ አቅራቢያ የተሰበሰቡ ሰልፈኞችን በአስለቃሽ ጭስ በተነ። ቬንዝዌላን ባናወጠው የመሬት መንቀጥቀጥ ቢያንስ የ164 ሰዎች ሕይወት መጥፋቱን 971 ሰዎች መጎዳታቸውን የሀገሪቱ ጊዜያዊ ፕሬዝደንት አስታወቁ። በርካታ ሃገራት ለእርዳታ እጃቸውን ዘርግተዋል። የኢራን አብዮታዊ ዘብ አዛዥ እስራኤል ከመላ ሊባኖስ መውጣት እንደሚኖርባት አመለከቱ። እስራኤል ሂዝቦላህ ትጥቁን ሳይፈታ ኃይሌን አላወጣም ብላለች። ፈረንሳይ ከሩሲያ ጋር ግንኙነት ያለው ነዳጅ ጫኝ መርከብን በሲሲሊ የባሕር ዳርቻ ላይ መያዟን አስታወቀች። ሩሲያ ድርጊቱን አውግዛ የባሕር ላይ ውንብድና ብላዋለች።
-
94
የሰኔ 17 ቀን 2018 የዓለም ዜና
-ራሱን የሊቢያ «የመረጋጋት መንግሥት» ብሎ የሚጠራዉ የምሥራቅ ሊቢያ ስብስብ የኢትዮጵያ፣ የሶማሊያ፣ የኤርትራና የሱዳን ዜጎች ሊቢያ እንዳይገቡ አገደ።---አዉሮጳን የገለበዉ የሙቀት ማዕበል የሰዎች ሕይወት እያጠፋ፣የትምሕርት ሒደት፣ሥራና እንቅስቃሴንም እያስተጓጎለ ነዉ።አለቅጥ የናረዉ ሙቀት ያንገበገባቸዉ አንዳድ ሰዎች ዘለዉ ወንዝ፣ኩሬና ገንዳ ዉስጥ እየገቡ ሞተዋል።--የዓለም የአዉቶሚክ ተቆጣጣሪ ድርጅት (IAEA) የኢራንን የኑክሌር ተቋማትና ንጥረ ነገር በቅርቡ እንደሚፈትሽ አስታወቀ።ኢራን ግን የኑክሌር ጉዳይ የሚነሳዉ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ያደረገችዉ ሥምምነት ገቢራዊነት ሲረጋገጥ ብቻ ነዉ ትላለች።
-
93
የሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ ም የዓለም ዜና
ግብፅ ከህገ-ወጥ የወርቅ ማዕድን ጋር በተያያዘ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በቁጥጥር ስር አዋለች።ዩጋንዳ ውስጥ አንድ አዲስ ሰው ላይ ኤቦላ ተረጋገጠ፤ በጠቅላላው 20 ሰዎች ተይዘዋል እስራኤል ወደፊት የጦር መሣሪያ አቅርቦትን በተመለከተ የዩናይትድ ስቴትስ ጥገኛ መሆን እንደማትፈልግ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ አስታወቁ። አምስት ልዑካንን ያቀፈ የታሊባን ቡድን ዛሬ ከአውሮጳ ህብረት ኮሚሽን ተወካዮች ጋር ለመምከር ብራስልስ ገባ። ዶይቸ ቬለ DW በየዓመቱ የሚያካሂደው ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙኃን መድረክ ዛሬ ማክሰኞ በቦን ከተማ መካሄድ ጀመረ።
-
92
የሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና
የኬንያ የሰራተኛ ጉዳይ ሚኒስትር፤ ወጣቶችን ለሩስያ በወታደርነት በመመልመል እንደሚጠረጠሩ ተገለጸ። በቀጠር በአንድ የተፈጥሮ ጋዝ ማምረቻ በደረሰ ፍንዳታ 13 ሰዎች ሲሞቱ በ 54 ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የቀጠር የሐገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። በዮናይትድ ስቴትስና ኢራን መካከል በስዊዘርላንድ ሲካሄድ የነበረ ንግግር በጥሩ መንፈስ መጠናቀቁን የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር አስታወቁ።የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር ከጠቅላይ ሚኒስትርነት ስልጣናቸውንና ከሌበር ፓርቲ መሪነታቸው በገዛ ፈቃዳቸው እንደሚለቁ አስታወቁ።
-
91
የሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
የዛሬው የዓለም ዜና በአብዛኛዎቹ አካባቢዎች ገዡ ፓርቲ ብልፅግና 90 በመቶ ድምፅ ማግኘቱን ምርጫ ቦርድ መግለጹን፣በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ነፃ እና ገለልተኛ ተቋም ሆኖ መስራቱን የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ መናገራቸውን፣በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሴቶች ያለስጋት እንዲሳተፉ ሁሉን አቀፍ ርምጃ ተወስዷል ሲል የኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር ማለቱን እና በምርጫ ወቅት ጥቃቶች መፈፀማቸውን መጠቆሙን እንዲሁም ገዥው ፓርቲ ብልፅግና በቀጣይ አምስት የስልጣን አመታት የነበሩ ችግሮችን እንዲቀርፍ ነዋሪዎች መጠየቃቸውን አካቷል። # ምርጫ2018 #EthiopiaElection2026
-
90
የሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና
• የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኤርትራ ጉዳይ ልዩ መርማሪ በሀገሪቱ የሰብአዊ መብት ጥሰት እየተባባሰ መምጣቱን አስታወቁ። • በእስር ላይ የነበረችው ጋዜጠኛ ሳልሳዊት ባይነሳኝ መፈታቷን ቤተሰቦቿ ለዶቼ ተናገሩ። • በምስራቃዊ ሊቢያ የባህር ዳርቻ የአንድ ህጻን ሴት ልጅን ጨምሮ በትንሹ የ15 ፍልሰተኞች አስከሬን ተገኘ። • አፍሪካ እና የካሪቢያን ሀገራት መሪዎች ጥቁሮችን ለባርነት የዳረጉ ያሏቸውን ሃገራት ካሳ እንዲከፍሉ ጠየቁ ። • ኢራን የሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥን በድጋሚ ዘጋች። • አውሮጳን እያናወጠ የሚገኘው አስከፊ የሙቀት ማዕበል በጀርመን ፣ፈረንሳይ እና ጣልያን ብርቱ ተጽዕኖ ማሳደሩ ተነገረ።
-
89
የሰኔ 12፣ ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና
• በትግራይ ክልል ለወታደራዊ ስልጠና የሚደረገው የአፈሳ ዘመቻ ብርቱ ትችት እና ተቃዉሞ መቀስቀሱ ተዘገበ ። • በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት ዛሬ ዓርብ አስጠነቀቀ። • እስራኤል እና የሊባኖሱ ታጣቂ ቡድን ሄዝቦላህ ቀደም ሲል አድርገው የነበረውን የተኩስ አቁም ስምምነት ለማደስ መስማማታቸው ተገለጸ። • የአውሮጳ ኅብረት መሪዎች በሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት ዙሪያ የኅብረቱን ጥቅሞች ለማስከበር ከሩስያ ጋር ቀጥተኛ ያልሆነ ግንኙነት ለመጀመር ያቀረቡት ሐሳብ ሳይሳካ ቀረ።
-
88
የሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
አርዕስተ ዜና -ዩናይትድ ስቴትስ «አክራሪ» ባለቻቸዉ የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አባላትና በቤተሰቦቻቸዉ ላይ ያነጣጠረ የቪዛ እገዳ ጣለች። ዩናይትድ ስቴትስ የቪዛ እገዳዉን የጣለችዉ / በትግራይ ክልል ሠላም ለማስፈን የተደረገዉን ስምምነት በሚጥሱና ከሚጥሱ ወገኖች ጋር በሚተባበሩ ሰዎች ላይመሆኑን አስታውቃለች። -የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባለፈዉ ግንቦት በተደረገዉ ምርጫ ሒደት ቅሬታ ከቀረበባቸዉ 128 የምርጫ ክልሎች ለ85ቱ ዉሳኔ መስጠቱን ዐሳወቀ። -በኤልኒኞ ምክንያት ኢትዮጵያውያን ጨምሮ 22 ሀገራት ለከፍተኛ አደጋ መጋለጣቸውን FAO እና የWFP ዛሬ በጋራ አሰሳቡ።
-
87
የሰኔ 10 ቀን 2018 የዓለም ዜና
-የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ ያስገነባችዉ ግድብ ግብፅን ለብዙ ችግሮች አጋልጧል አሉ።ትራምፕ የግብፅ አቻቸዉን ዛሬ ሲያነጋግሩ እንዳሉት መስተዳድራቸዉ ሁለቱን ሐገራት ለማግባባት እንደሚጥር አስታዉቀዋልም።---በ13 ሐገራት ወይም ግዛቶች የሚኖር በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ሕዝብ አስቸኳይ ርዳታ ካላገኘ ለአስከፊ ረሐብ እንደሚጋለጥ የተባበሩት መንግሥታት ሁለት ድርጅቶች አስታወቁ።ድርጅቶቹ እንደሚሉት ሱዳን፣ ሶማሊያና ጋዛን ጨምሮ ለችግር የተጋለጡ 266 ሚሊዮን ሰዎች በቂ ርዳታ አያገኙም።---የቡድን 7 አባል ሐገራት መሪዎች በማደግ ላይ ባሉ ሐገራት ላይ ያለዉን ዕዳ ለማቃለል ቃል ገቡ።
-
86
የሰኔ 9 ቀን 2018 የዓለም ዜና
በዚምባብዌ አንድ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ከባቡር ጋር በመላተሙ ቢያንስ 9 ሰዎች ሲሞቱ 25 መቁሰላቸውን የሐገሪቱ የሐገሪቱ ባለስልጣናት አሳወቁ። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሐገራቸው ከአሜሪካ ጋር የመጨረሻው የሰላም ስምምነት በመጨው አርብ በስዊትዘርላንድ እንደሚፈረም አረጋገጡ።ዩክሬን በሞስኮ አቅራቢያ የሚገኘውን የሩስያ የነዳጅ ማጣሪያ ማጋየቷ ተሰማ። ጀርመን ወደ 30 የሚሆኑ የአፍጋኒስታን ዜጎች ከሐገር ማባረሯን አሳወቀች።
-
85
DW Amharic የሰኔ 08 ቀን 2018 የዓለም ዜና
ከደሴ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ የሕዝብ ማጓጓዣ አውቶቡስ 170 ሜትር ርዝመት ያለው ገደል ውስጥ በመውደቁ የ31 ሰዎች ሲሞቱ 30 ሰዎች ከባድና ቀላል ጉዳት ደረሰባቸው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከቢሾፍቱ አቅራቢያ እየተገነባ በሚገኘው አውሮፕላን ማረፊያ ምክንያት “የሚጎዳ አርሶ አደር” እንደማይኖር ቃል ገቡ። የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽነር ፎልከር ቱርክ በሱዳን ጦርነት የድሮን አጠቃቀም ላይ የታየውን “ከፍተኛ ጭማሪ” አወገዙ። ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን የገጠሙትን ጦርነት ለማብቃት ከሥምምነት መድረሳቸውን አሳወቁ። ሩሲያ በዩክሬን ከተሞች ላይ በሚሳይሎች በፈጸመችው ጥቃት11 ሰዎች ተገደሉ።
-
84
የሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና
የሶማሊላንድ ፕሬዝደንት አብዲራሕማን ሞሐመድ አብዱላሒ "ታሪካዊ" የተባለለትን ጉብኝት እውቅና በሰጠቻቸው ሀገር እስራኤል እያደረጉ ነው። በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብቻ ከ 700 በላይ ሰዎች በኢቦላ ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ። የእስራኤል ጦር ዛሬ የሂዝቦላህ ቡድንን ለማጥቃት የሊባኖስ ዋና ከተማ ቤይሩት ደቡባዊ ክፍልን ከአየር ደበደበ። ቡድኑ አስቀድሞ ዛሬ ጠዋት በሰሜናዊ እስራኤል የድሮን ጥቃት ፈፅሟል። የኢራን ዋና ተደራዳሪ ሞሐመድ ባግኸር ጋሊባፍ በዚህ አይነት ሁኔታ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር የሰላም ድርድሩን መቀጠል ፋይዳ እንደማይኖረው ተናገሩ።
-
83
የሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና
• የኤርትራው የማስታወቂያ ሚንስትር የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ብልጽግና ፓርቲ በተዛባ መረጃ ላይ የተመሰረተ ፕሮፖጋንዳ ያሰራጫል ሲሉ ከሰሱ ። • በኢራን እየተካሄደ ያለው ጦርነት የአውሮፕላን ነዳጅ ዋጋን በመናርና የአቅርቦት እጥረትን በመፍጠር በአፍሪካ አየር መንገዶች ላይ ከፍተኛ ቀውስ እየደቀነ መሆኑን የአፍሪካ አየር መንገዶች ማኅበር (AFRAA) አስጠነቀቀ። • ዩጋንዳ በኤቦላ ወረርሽኝ ምክንያት በአሜሪካ እና በሌሎች ሀገራት የተጣለባትን የአየር ጉዞ እገዳ «ኢ-ፍትሐዊ» ስትል ኮነነች። • የኒጀር ወታደራዊ ሁንታ ግብረ-ሰዶማዊነትን በወንጀል የሚቀጣ አዲስ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ማውጣቱን አስታወቀ።
-
82
የሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
በአፍሪቃ ሕብረት የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ተወካይ የተመራ የልዑካን ቡድን ወደ መቀለ መጓዙ ተሰማ። የቡድኑ መሪ የጉዟቸው ዓላማ ሁኔታዎች እንዳይባባሱ አስቀድሞ ለማርገብ ነው ብለዋል። የትግራይ ክልል ባለሥልጣናት ለዳግም ጦርነት እየተዘጋጁ ነው መባሉን ውድቅ ማድረጋቸው ተዘገበ። «ላ ክሯ» ለተሰኘ ጋዜጣ የምትዘግብ ፈረንሳዊት ጋዜጠኛ ከኢትዮጵያ መባረሯን ድርጅቱ አመለከተ። የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን አሾልካ አወጣች ያሉት የስምምነት በጽሑፍ ያለውን ውል የሚወክል አይደለም አሉ። የኢራን ባለሥልጣናት በበኩላቸው ጣላቶቻችን ያሏቸው አሜሪካን እና እስራኤል ከኃይል በቀር የድርድር ቋንቋ አይገባቸውም ብለዋል።
-
81
የሐሙስ ሰኔ 4 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
መቐለ፥ ደብረፅዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር) ኦሉሴጉን ኦባሳንጆን ዛሬ መቐለ ከተማ ዉስጥ ተቀብለው አነጋገሩ፤ አ.አ፥ ለ2019 ዓ.ም የበጀት ዓመት ከ2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ለፕላን-በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተመራ፤ ጂዳ፥ ሣዑዲ ዓረቢያ ታስረው የነበሩ 1,655 ኢትዮጵያውያን ምሕረት አገኙ፤ የአሜሪካ ጦር በሁለተኛው ቀን ኢራን ውስጥ በርካታ ኢላማዎችን እየመታ መሆኑን ዐሳወቀ፤ ኬፕታውን፥ የኬፕ ታውን ማራቶን ከዓለማችን ታላላቅ የማራቶን ውድድሮች መካከል አንዱ ኾነ፤ ሜክሲኮ ሲቲ፥ የዓለም እግር ኳስ ጨዋታ በደቡብ አፍሪቃ እና በሜክሲኮ መካከል ዛሬ ማታ ይከፈታል
-
80
የሰኔ 3 ቀን፣ 2018 የዓለም ዜና
-ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክና ዩጋንዳ ዉስጥ የተሰራጨዉ የኢቦላ ተሕዋሲ የያዛቸዉ ሰዎች ቁጥር 620 ደረሰ።ተሕዋሲዉ 120 ያክል ሰዎች መግደሉ ተረጋግጧል።ሶስት የኮንጎ ቤተ-ምርመራዎች ተሕዋሲዉን መመርመሪያ መሳሪያና ንጥረ-ነገር አልቆባቸዋል።---ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን እንዳዲስ መደባደብና መዛዛት ይዘዋል።የዩናይትድ ስቴትስ ጦር የኢራን ወታደራዊ ተቋማት ያላቸዉን ሥፍራዎች ሲደበድብ፣ ኢራን ባፀፋዉ ከባሕሬን እስከ ዮርዳኖስ የሚገኙ የዩናይትድ ስቴትስ የጦር ሠፈሮችን ደብድባለች።----ዩናይትድ ስቴትስ እንዳይገባ የተከለከለዉ ሶማሊያዊ ዓለም አቀፍ የእግር ኳስ ግጥሚያ ዳኛ ሞቃዲሾ ሲመለስ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት።
-
79
የዓለም ዜና፤ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ማክሰኞ
አርስተ ዜና--በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የተፈናቃዮች ልዩ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በአማራ ክልል ዛሬ ተከናወነ። ከኦሮሚያ ክልል ምስራቅና ምዕራብ ወለጋ እንዲሁም በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል በነበሩ የፀጥታ ችግር ተፈናቃዮች ወደ ቤታቸዉ እንዲመለሱ ጠይቀዋል።-በኢትዮጵያ ፌደራል መንግስትና በህወሓት መካከል ተባብሶ እንደቀጠለ የተገለፀውን ውጥረት በተመለከተ፣ የፕሪቶሪያውን ግጭት በዘላቂነት የማቆም የሰላሞ ስምምነት በዋነኛነት ከመራው የአፍሪቃ ኅብረት በኩል እስካሁን የወጣ መግለጫም ይሁን የተሰጠ አስተያያት የለም።-የዓለም ዋንጫ ጨዋታን ለመምራት ለሀገሩ የመጀመሪያው ለመሆን የተዘጋጀው ሶማሊያዊ ዳኛ ወደ አሜሪካ እንዳይገባ ተከለከለ።
-
78
የሰኞ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
የደቡብ አፍሪቃው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ደቡብ አፍሪቃ በሚገኙ ስደተኞች ላይ ከሕግ በላይ ሆነው እርምጃ የሚወስዱትንሰዎች ባለሥልጣናቶቻቸውእንደማይታገሱ አሳሰቡ ። ኢራን እስራኤልን ትናንትናና ዛሬ ስትደበድ እሥራኤልም በአጸፋው ኢራንን ዛሬ መታለች ። ትናንት ወደ እሥራኤል ሮኬቶችን በተመተኮስ ማጥቃት የጀመረችው ኢራን 24 ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የመከላከል ዘመቻውን እንደምታቆም አስታውቃለች። ከእሁዱ የኢራን ጥቃት በኋላ የእሥራኤል ጦር ዛሬ (መጠነ ሰፊ) ያለውን ጥቃት በኢራን ላይ መፈጸሙን ገልጿል። ማልታ አቅራቢያ በሰጠመች ጀልባ ውስጥ የነበሩ ቢያንስ 11 ስደተኞች ሞቱ። ወደ 50 የሚሆኑ ደግሞ ተረፉ።
-
77
የግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
የማዕከላይ አፍሪካ ሪፐብሊክ መንግስት ከአሜሪካ የሚጠረዙ ስደተኞችን ተቀብሎ ለማስተናገድ መስማማቱን ከሐገሪቱ የወጡ ዲፕሎማሲያዊ ምንጮች አረጋገጡ። ዩናይትድስቴትስና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱት ጦርነት ዛሬ 100 ቀናትን ደፍኗል። ዩናይትድ ስቴትስ በተለያዩ ባንኮች ታግዶ የሚገኘውን የኢራን ሐብት፤ በኢራን የሚሳይልና የድሮን ጥቃት ለደረሰባቸው የባህረ ሰላጤ ሀገራት እንዲውል ማቀዷን አስታወቀች።
-
76
DW Amharic-የቅዳሜ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
የዛሬው የዓለም ዜና ፣የኢትዮጵያ አየር ሃይል በትግራይ ክልል ሸራሮ ከተማ አቅራቢያ አካሄደው በተባለው የድሮን ጥቃት ጉዳት ደረሰ መባሉን።ናይጄሪያ እና ጋና ዜጎቻቸው ደቡብ አፍሪካን ለቀው እንዲወጡ ሀሳብ ማቅረባቸውን፣ኩዌት፤ አዲሱ የኢራን ጥቃት 'አደጋ የሚያባብስ ' መሆኑን መግለጿን።በጀርመን በፖለቲካዊ መነሻ የሚፈጸም ወንጀል በከፍተኛ ደረጃ ጨምሯል መባሉን፣የሮማው ሊቃነ ጳጳስ በዓለም ላይ ዋልታረገጥነ አስተሳሰብ እንዲያበቃ ጥሪ ማቅረባቸውን እንዲሁም ኢራን ቅዳሜ ዕለት ቱርክን ለቀው ወደ ሜክሲኮ ከሚያመሩት ተጫዋቾቿ ጋር ለሚጓዙት የዓለም ዋንጫ ቡድን የድጋፍ ሰራተኞች ቪዛ በመከልከሏ አሜሪካን ክፉኛ መቸቷን አካቷe።
-
75
የዓለም ዜና፤ ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም አርብ
አርስተ ዜና-አሜሪካ በኩባ ላይ ተጨማሪ ማዕቀብ አሳረፈች። --ቅድሚያ ለሰብአዊ መብት የተባለ አገር በቀል የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት ዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ በትግራይ እየተካሄደ ነው ባለው አስገዳጅ ወታደራዊ ምልመላን እንዲያወግዝ እና እንዲያስቆም ጥሪ አቀረበ።--በደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በቡርጂ እና ጌዴኦ ዞኖች ምርጫ ሲያጭበረብሩ የተገኙ ከስድስት እስከ አሥር ወር እሥራት ተቀጡ ፡፡--የቀድሞ የአዲስ አበባን ከንቲ አምባሳደር ዓሊ አብዶ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።--የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ከአራት ዓመታት በላይ የዘለቀው ጦርነት እንዲያበቃ ስምምነት ላይ ለመድረስ ለፑቲን ግልፅ ደብዳቤ ፃፉ።
-
74
የግንቦት 27 ቀን 2018፤ ዓለም ዜና
በዛሬው የዓለም ዜና ተቃዋሚው የቁጫ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በክልሉ ምርጫ«የማጭበርበር ተግባራት ተፈጽሟል» ሲል ቅሬታ ማቅረቡን።የምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ)በሶማሊያ መዲና ሞቃዲሾ የተከሰተዉ ሁከት በጥልቅ እንዳሳሰበው ማስታወቁ።በዓለም ላይ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች ችላ ተብለዋል ሲል አንድ የእርዳታ ድርጅት መግለጹን።ሊባኖስ፤ የእስራኤል የድሮን ጥቃቶች መቀጠላቸውን መግለጿ።ኩዌት የኢራን ድሮን አውሮፕላን ማረፊያዋን መምታቱን ማስታወቋን።የአሜሪካ ሕግ አውጪዎች ሀገሪቱ በኢራን የምታደርገውን ወታደራዊ እርምጃ ለማስቆም የቀረበውን ውሳኔ መደገፋቸውን የሚያስቃኙ ዜናዎች የሚሉት ተካተዋል።
-
73
የግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
የግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን እየሰፋ መጣ ያሉትን ጥቃት የመንግሥት የፀጥታ አካላት ያላቸውን መዋቅር ተጠቅመው እንዲያስቆሙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያርክ ጠየቁ። በኢትዮጵያ የአውሮጳ ኅብረት ልዑክ እና በአዲስ አበባ የሚገኙ የኅብረቱ አባል ሃገራት ኤምባሲዎች ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ምርጫ ያልተካሔደባቸው የምርጫ ክልሎች ድምፅ የመስጠት «ዕድል ይሰጣቸዋል» የሚል ተስፋ እንዳላቸው አስታወቁ። ዴሞክራቲክ ኮንጎ ውስጥ በኢቦላ መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር 343 ደረሰ። ኢራን በመካከለኛው ምሥራቅ በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ ጥቃት ቀጥላለች።
-
72
የዓለም ዜና፤ ግንቦት 25 ቀን 2018 ማክሰኞ
-አርሰተ ዜናዎች--ሩሲያ በዩክሬን ላይ በድጋሚ በሰነዘረችዉ ከፍተኛ ጥቃት ቢያንስ አስር ሰዎች ተገደሉ ከ100 በላይ ሰዎች ደግሞ ቆሰሉ።-በኢትዮጵያ የተካሄደው የሰባተኛው አጠቃላይ ምርጫ የድምፅ ቆጠራ ውጤት፣ በምርጫ ጣቢያዎች እየተለጠፈ ይገኛል።--በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ሀገረ ስብከት በአስኮ ወረዳ በሺርካ ወረዳና ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 13 ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያኖች መገደላቸውን ሀገር ስብከቱ አመለከተ። የመቶ አንድ ዓመት እድሜ እንደነበረው የተገለጸው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያንም ሙሉ በሙሉ በእሳት መጋየቱ ተነግሯል።
-
71
DW Amharic የግንቦት 23 ቀን 2018 የዓለም ዜና
የጋምቤላ ክልል ፖሊስ “የተለየ የይለፍ ፈቃድ ካልተሰጠ በቀር” ማንኛውም ተሽከርካሪ ከዛሬ ጀምሮ ለሦስት ቀናት መንቀሳቀስ እንደማይችል አስታወቀ። በምሥራቃዊ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አምስት ሕሙማን ከኢቦላ ማገገማቸውን የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴድሮስ አድኃኖም ተናገሩ። ኢራን ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው ድርድር የኑክሌር የጦር መሣሪያ ላለመስራት መስማማቷን የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ገለጹ። የኢራን ዋና ተደራዳሪ ሞሐመድ ባግኸር ጋሊባፍ ግን “የኢራናውያን መብቶች መከበራቸውን ሳናረጋግጥ አንዳች ሥምምነት አናጸድቅም” ብለዋል።
-
70
የግንቦት 22 ቀን 2018 ፤የዓለም ዜና
የዛሬው የዓለም ዜና፤የአማራ ፋኖ የጣለው የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ ገደብ የምርጫ ሥራዉን ስለማስተጎጎሉ የደረሰው መረጃ እንደሌለ ምርጫ ቤርድ ማስታወቁ፣የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር የኢቦላ ወረርሽን ወደተቀሰቀሰባት ዲሞክራቲክ ኮንጎ ማምራታቸውን፣ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ ነዋሪዎች አካባቢውን እንዲለቁ ትዕዛዝ መስጠቷን፣ በጀርመን የሙኒክ አውሮፕላን ማረፊያ አጠራጣሪ ድሮን መታየቱን ተከትሎ ለአጭር ጊዜ በረራ መቋረጡን አሜሪካ ስምምነት ላይ ካልደረሰ በኢራን ጦርነቱን እንደገና ለመጀመር ዝግጁ መሆኗን መግለጿን፣እንዲሁምሩሲያ፤ በአርሜኒያ የሚገኙ አምሳደሯን መጥራቷን አካቷል።
-
69
የግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
ከአማራ ክልል መንገደኞችን ጭኖ ትናንት ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ አውቶብስ ላይ በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት በርካቶች መገደላቸው ተሰማ። ማዕከላዊ ኬንያ ውስጥ በሚገኘው የሴቶች አዳሪ ትምህርት ቤት የተነሳውን እሳት በመለኮስ የተጠረጠሩ ስምንት ተማሪዎች መያዛቸውን ፖሊስ አስታወቀ። የኬንያ ፍርድ ቤት በሀገሪቱ በኤቦላ ተሐዋሲ ለተያዙ የአሜሪካ ዜጎች አግልሎ ማቆያ የማዘጋጀት እቅድን በጊዜያዊነት አገደ። ኢራን ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ለገባችበት ውዝግብ ለታሰበው የሰላም ስምምነት ከቃል ይልቅ ተግባር እንደምትፈልግ አስታወቀች።
-
68
DW Amharic የግንቦት 20 ቀን 2018 የዓለም ዜና
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ በጥሞና ወቅት “ፕሮጀክት ማስጀመር እና ማስመረቅ” ከለከለ። ክልከላው የምርጫውን ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ያግዛል በተባለው የጥሞና ጊዜ ከማይደረጉ እንቅስቃሴዎች ውስጥ የተካተተ ነው። ከኢትዮጵያ መንግሥት የሚዋጋው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ከነገ ጀምሮ በአማራ ክልል “ለተከታታይ አምስት ቀናት ከአንቡላንሶች በስተቀር ሁሉም መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ መደረጋቸውን” አስታወቀ። የኢትዮጵያ መንግሥት አገሪቱ አንድ ቢሊዮን ዶላር የተበደረችበት ቦንድ ባለቤቶችን ከሚወክል ጊዜያዊ ኮሚቴ ጋር ያደረገው ውይይት ውጤታማ ሳይሆን መቅረቱን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።
-
67
የረቡዕ ግንቦት 19 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
አ.አ፥ ለቀጣዩ ምርጫ ሥራ ዝግ እንደሚኾን ምርጫ ቦርድ ዐሳወቀ፤ አ.አ፥ 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በመላ ኢትዮጵያ ተከበረ፤ ጆሐንስበርግ፥ የጋና መንግሥት ዜጎቹን መጤ ጠል ሥጋት ካጠላባት ደቡብ አፍሪቃ ወደ አገራቸው እየመለሰ ነው፤ ዋሽንግተን፥ ካናዳ እና ባሐማ ከኤቦላ ጋር የተገናኘ የጉዞ ክልከላ ተግባራዊ አደረጉ፤ ናይሮቢ፥ ካናዳ እና ባሐማ ከኤቦላ ጋር የተገናኘ የጉዞ ክልከላ ተግባራዊ አደረጉ፤ ጋዛ፥እሥራኤል አዲስ የተሾሙ የሐማስ ወታደራዊ ክንፍ አዛዥን መግደሏን ዐሳወቀች፤
-
66
የግንቦት 18 ቀን 2018 ዓም የዓለም ዜና
የግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና በሱዳኑ ጦርነት ከፈጥኖ ደራሹ ኃይል በምህጻሩ RSF ጎን ተሰልፈው የሚዋጉ ኮሎምብያውያን የግል ቅጥረኛ ወታደሮችን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ታሰለጥናለች ሲል ሂዩመን ራይትስ ዋች አስታወቀ ። በኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እጎ ዩጋንዳ ዉስጥ ተጨማሪ ሰዎች በኢቦላ ተሕዋሲ መያዛቸዉን የሁለቱ ሐገራት የጤና ባለሥልጣናት አስታወቁ። ኢራን፣ ዩናይትድ ስቴትስ ትናንት የፈጸመችባትን የአየር ድብደባ አወገዘች። ድብደባዎቹን የተኩስ አቁሙን የጣሰ ሲል ያወገዘው የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት፣ ጥቃቶቹ ለሚያስከትሉት መዘዞች ሁሉ ዋሽንግተን ሃላፊነቱን እንደምትወስድ አስጠንቅቋል።
-
65
የግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
መገናኛ ብዙኃን ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በመንግሥት ቁጥጥር ስር በሆነበት፤ አመጽና ዛቻን በመጋፈጥ፤ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. በሚካሄደው ምርጫ እንደሚሳተፉ ተዘገበ። ዓለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ተልእኮ የወታደሮች ቁጥር በመቀሱ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን አንድ ጥናት አመለከቱ። ኢራን በመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነቱን ለማስቆም ከአሜሪካ ጋር የምታካሄደው ድርድር መሻሻሎች ቢኖሩትም ስምምነት ላይ ገና አልተደረሰም አለች። ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው ከኢራን ጋር የሚደረገው ስምምነት ወይ ታላቅና ትርጉም ያለው ይሆናል ወይ ደግሞ ስምምነት አይኖርም ብለዋል።
-
64
የግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና
• በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የኢቦላ ወረርሽኝ የሟቾች ቁጥር 204 ደረሰ። ኢትዮጵያን ጨምሮ 10 የአፍሪካ ሀገራት ወረርሽኙ አስግቷቸዋል። • አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱን ለማቆም የሚያስችላቸው ስምምነት ላይ ለመድረስ መቃረባቸው ተሰማ። • ሩሲያ ዛሬ ሌሊት በዩክሬን መጠነ-ሰፊ የድሮን እና የሚሳኤል ጥቃት “ኦሬሽኒክ” የተሰኘውን የሃይፐርሶኒክ ባሊስቲክ ሚሳኤል • በፓኪስታን በደረሰ የአጥፍቶ ጠፊ የቦምብ ጥቃት የ23 ሰዎች ህይወት አለፈ። • ኢትዮጵያዉያን አትሌቶች ዛሬ ደቡብ አፍሪቃ ኬፕታውን ውስጥ የተደረገውን የማራቶን ሩጫ የቦታውን ክብረ ወሰን በማሻሻል ጭምር አሸነፉ ።
-
63
የግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎና ኡጋንዳ በተጨማሪ 10 የአፍሪካ ሐገራት የኢቦላ ቫይረስ ሥርጭት እንደሚያሰጋቸው የአፍሪካ የበሽታዎች መከላከያና መቆጣጠሪያ ድርጅት አስታወቀ። ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን ላይ ዳግም ጦርነት የምታውጅ ከሆነ ብርቱ አጸፋዊ ምላሽ እንደምትሰጥ ኢራን አስጠነቀቀች። በሰሜን ቻይና በምትገኝ የሻንዚ ግዛት በአንድ የከሰል ማዕድን ማውጫ ትላንት ባጋጠመ ፍንዳታ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ቢያንስ 90 መድረሱን ተሰማ። ዩክሬይን በሩስያ ቁጥጥር ሥር በሚገኘው እና የቀድሞ ግዛቷ በነበረው ሉጋንስክ ከተማ ፈጸመችው በተባለ የድሮን ጥቃት 18 ሰላማዊ ሰዎች ሲሞቱ 48 መቁሰላቸውን የአካባቢው የሩስያ ገዢ አስታወቁ።
-
62
የዓለም ዜና፤ ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም አርብ
አርስተ ዜና -የደቡብ አፍሪቃ ባለስልጣናት ተባብሶ የቀጠለዉን ጥቁር የውጭ ዜጋ ጥላቻን ተከትሎ ጥቃትን በመፍራት ደርባን በሚገኘ አንድ የቤተክርስቲያን ማእከል ዉስጥ ከለላ የጠየቁ አፍሪቃዉያን ከማዕከሉ አስወጡ። ኢትዮጵያዉያንም ይገኙበታል።-ህንድና የአፍሪቃ ህብረት በሚቀጥለው ሳምንት በኒው ደልሂ ሊያካሂዱት የነበረው የመሪዎች ጉባዔ በኮንጎ በተቀሰቀሰዉ የኢቦላ ወረርሽኝ ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ ተራዘመ። -የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮ ፈረንሳይ በቅኝ ግዛቶቿ የነበረውን ባርነት ለመቆጣጠር ያገለገሉትን ያረጁ ህግጋቶች እንድታስወግድ እንደሚፈልጉ ተናገሩ። ሕግጋቱ አገራቸዉ ዛሬ ከምትላቸው እሴቶች ጋር አይጣጣሙም ብለዋል።
-
61
የግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
የግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ (ኦፌኮ) ለመንግሥት አቅርቦት የነበረው ጥያቄ አጥጋቢ ምላሽ ባለማግኘቱ በምርጫው ተሳትፎው እጅግ የተቀዛቀዘ እንዲሆን ማድረጉን አስታወቀ ። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የትምህርት ቢሮ በክልሉ የ2018 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን ከታቀደው አንድ ወር ቀደም ብሎ እንደሚያበቃ አስታወቀ። ባለፉት 3 ሳምንታት ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ፣ ዩጋንዳ ወይም ደቡብ ሱዳን የነበሩ አሜሪካውያን ጠለቅ ላለ ምርመራ ፣በዋሽንግተን ዳላስ አውሮፕላን ማረፊያ በኩል ብቻ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ እንዲገቡ የአሜሪካን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳሰበ ።
-
60
የግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲ «አለአግባብ ከምርጫው ተሳትፎ አግልሎኛል» ያለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ላይ ክስ መሠረተ። ምርጫ ቦርድ በበኩሉ የዕጩዎችን ምዝገባ አጠናቅቄ የድምፅ መስጫ ወረቀት ኅትመት ጀምሬያለሁ ይላል። የአውሮጳ ሕብረት ኮሚሽን ከጎርጎሪዮሳዊው 2024 ዓ,ም ጀምሮ ኢትዮጵያ ላይ ጥሎት የቆየው የቪዛ ገደብ መነሳቱን አስታወቀ። የዓለም የጤና ድርጅት በኤቦላ መሞታቸው የተጠረጠረ ሰዎች ቁጥር 139 መድረሱን ዛሬ አስታወቀ። በተሐዋሲው መያዛቸው የተጠረጠረም 600 ደርሰዋል። ሩሲያና ቻይና ለዩክሬን ጦርነት መንስኤ የሆኑ መሠረታዊ ነገሮች እንዲወገዱ ጥሪ አቀረቡ። በኢራን ላይ የሚደርሰውን ጥቃትም ኮነኑ።
-
59
የማክሰኞ ግንቦት 11 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
መቐለ፥ «የትግራይ የሰላምና ለውጥ ምክር ቤት» ምሥረታን ሕወሓት አጣጣለ፤ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ዐቃቢያነ-ሕግጋት ከፊል የሥራ ማቆም አደረጉ፤ ኪንሻሳ፥ የኢቦላ ወረርሺኝ አኅጉራዊ የጤና ሥጋት መኾኑ ታወጀ፤ ቤርሊን፥ አሜሪካዊ የኮሮና ታማሚ ጀርመን ለልዩ ኅክምና ተወሰደ፤ ሞስኮ፦ ቤላሩስ ከሩስያ ጋር የኑክሊየር ጦር መሣሪያን የሚያካትት ወታደራዊ ልምምድ መጀመሯን ይፋ አደረገች፤ ካይሮ፥ የአፍሪቃ ዋንጫ ማጣሪያ ድልድል ይፋ ኾነ
-
58
የዓለም ዜና፤ ግንቦት 10 ቀን 2018 ዓ.ም ሰኞ
አርስተ ዜና፦ በኬንያ የነዳጅ ዋጋ ላይ ከፍተኛ የተባለ ጭማሪ በመደረጉ አገር አቀፍ የትራንስፖርት አድማ ተቀሰቀሰ። ናይሮቢን ጨምሮ በተለያዩ ከተሞች ሕዝባዊ ተቃዉሞዉ ቀጥሏል። -ለአፍሪቃ ቀንድ ሰላም እንዲሰሩ በድጋሚ የተሾሙት የቀድሞው የናይጀሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ፣ በኢትዮጵያ ፌደራል መንግስትና በህወሓት መካከል ያለውን ልዩነት በበለጠ ብልሃትና ስልታዊ አካሄድ መፍታት እንደሚገባቸው ተመለከተ።-የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ቴህራን ላይ ጫና በማሳረፍ ስምምነት ላይ ካልተደረሰ ኢራን ትወድማለች" ሲሉ በድጋሚ ዛቱ።-በፈረንጆቹ 2025 ዓመት በዓለም ላይ ከፍተኛ ቁጥር የሞት ቅጣት መፈፀሙን፤ አምነስቲ አስታወቀ።
-
57
DW Amharic- የግንቦት 09 ቀን 2018 የዓለም ዜና
በዛሬው የዓለም ዜና የዓለም ጤና ድርጅት በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በt,ከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ ምክንያት ዓለም አቀፍ የአስኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጁን፣በናይጄሪያ ወታደራዊ ትምህርት ቤት ላይ በተፈፀመ የአክራሪዎች ጥቃት 17 የፖሊስ ሰልጣኞች መገደላቸውን፣በዩናይትድ አረብ ኤሜሬትስ የኒኩሌር ማዕከል ተፈጸመ በተባለ የድሮን ጥቃት በማዕከሉ ላይ ምንም ጉዳት አለመድረሱን፣ አሜሪካ ለኢራን የድርድር ሀሳብ በሰጠችው ምላሽ ላይ ምንም አይነት ተጨባጭ የስምምነት ሀሳብ የለውም ሲሉ የኢራን መገናኛ ዘዴዎች መግለፃቸውን እንዲሁም የሰሜን ኮሪያ የሴቶች የእግር ኳስ ቡድን በደቡብ ኮሪያ ጉብኝት ማድረጉን አካቷል።
-
56
DW Amharic የግንቦት 08 ቀን 2018 የዓለም ዜና
ኤርትራ እና ግብጽ የባሕር ትራንስፖርት የትብብር ሥምምነት ዛሬ ቅዳሜ በአስመራ ተፈራረሙ። ሥምምነቱ የተፈረመው የኤርትራ ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ እና የግብጽ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ በተገኙበት ነው። በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ኢቱሪ ግዛት በኢቦላ ወረርሽኝ ቢያንስ 80 ሰዎች ሞቱ። የቦኮ ሐራም አባላት ሳይሆኑ አይቀሩም የተባሉ ታጣቂዎች በሰሜን ምሥራቅ ናይጄሪያ ቦርኖ ግዛት ውስጥ በሚገኝ ትምህርት ቤት ከፈጸሙት ጥቃት በኋላ ቢያንስ 42 ልጆች ደብዛቸው መጥፋቱን የአካባቢው ተመራጭ ተናገሩ። የሐማስ ወታደራዊ ክንፍ አዛዥ ኢዚዲን አል-ሐዳድ ተገደሉ።
-
55
የግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
የግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና -በደቡብ አፍሪካ የመጤ ጠል እንቅስቃሴ ጋብ አያለ ቢመጣም «ሕገ ወጥ ግንባታ» በሚል ምክንያት ሱቆቻቸው እየፈረሱባቸው እንደሚገኙ ፍልሰተኛ ኢትዮጵያዊያውያን ለዶቼቬለ ተናገሩ ። -በኮንጎዋ ኢቱሪ ክፍለ ሀገር በተከሰተ አዲስ የኤቦላ ወረርሽኝ 65 ሰዎች መሞታቸውን መታወቁን የአፍሪቃ የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል አስታወቀ። -የብሪክስ አባል ሀገራት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ለሁለት ቀናት ኒው ዴልሂ ህንድ ውስጥ ያካሄዱትን ጉባኤ የጋራ መግለጫ ሳያወጡ ዛሬ አበቁ።
-
54
የዓለም ዜና፤ ግንቦት 6 ቀን 2018 ሐሙስ
አርስተ ዜና -የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቻይና በፕሬዚዳንት ዢ ከፍተኛ አቀባበል ተደረገላቸዉ። ትራምፕ አስደናቂ መሪ ሲሉ ዢ ጂንፒንግን አሞካሽተዋቸዋል። የሁለቱ ሀገራት "የተረጋጋ" ግንኙነት ለዓለም ፋይዳ እንደሚሆን የተናገሩት ዢ ጂንፒንግ በበኩላቸዉ፤ የታይዋን ጉዳይ በአግባቡ ካልተያዘ ግን ግጭት ሊፈጠር ይችላል ሲሉ አስጠንቅቀዋል።-ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጋር በተያያዘ በዩናይትድ ስቴትስ ከ4 ዓመታት በፊት ኢትዮጵያ ላይ ተጥሎ የቆየው የጦር መሣሪያ ማዕቀብ መነሳቱ ተገለፀ። ዩናይትድ ስቴትስ ኤርትራ ላይ የጣለችዉን ማእቀብ ለማንሳት እያሰበች እንደሆን ያስታወቀችዉ በዚሁ ሰሞን እንደሆን የሚታወስ ነዉ።
-
53
የግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
ትናንት ከአሶሳ ወደ መተከል ዞን ግልገል በለስ ከተማ ይጓዙ በነበሩ ተሽከርካሪዎች ላይ በተፈጸመ የታጣቂዎች ጥቃት የበርካቶች ሕይወት አለፈ። የፈረንሳይ ፕሬዝደንት ማኑዌል ማክሮ በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ ገብተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከፈረንሳዩ መሪ ጋር በጋራ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የሁለትዮሽ ውይይት ማካሄዳቸውን በማኅበራዊ መገናኛ ገጻቸው አመልክተዋል። ጋና ከደቡብ አፍሪቃ 300 ዜጎቿን ልታወጣ መሆኑን የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ዛሬ ከቀትር በኋላ ቻይና ገብተዋል። የትራምፕ ጉዞ በ9 ዓመት በአሜሪካ ፕሬዝደንት ወደ ቻይና የተደረገ የመጀመሪያ ጉብኝት ነው።
-
52
የግንቦት 4 ቀን 2018 የዓለም ዜና
-አርዕስተ ዜና -በጅቡቲ ወይም በሶማሊያ በኩል የአደን ባሕረ-ሠላጤን አቋርጠዉ ወደ አረብ ሐገራት ለመሰደድ የሚሞክሩ በርካታ ኢትዮጵያዉያን ቢሞቱም፣ ሌሎች መሰደዳቸዉን አለማቆማቸዉን ዓለም አቀፉ የፍልስተኞች ድርጅት አስታወቀ።-የዩናይትድ ስቴትስ ዉጪጉዳይ ሚንስትር ማርኮ ሩቢዮ ምሥራቅ አፍሪቃ ዉስጥ የሚደረጉ ግጭቶችን ለማስወገድ ኢትዮጵያ «ጠቃሚ» ያሉትን ሚና እየተወጣች ነዉ በማለት አደነቁ።--ፈረንሳይ ከአፍሪቃ ሐገራት ጋር ያላትን ወዳጅነት በአ,ዲስ መልክ እንደምታጠናክር አስታወቀች።ፈረንሳይ ከቀድሞ ቅኝ ግዛቶችዋ ከፈረንሳይኛ ተናጋሪ የምዕራብ አፍሪቃ ሐገራት ጋር ከተቃቃረች ወዲሕ ፊቷን ወደ እንግሊዝኛ ተናጋሪዎቹ አዙራለች
-
51
የግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
የግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሦስተኛ የፀረ ሽብር እና ሕገ መንግሥታዊ ጉዳዮች ችሎት ፣የክስ ሂደታቸው "በኘላዝማ" እንዲታይ ተወስኖባቸው የነበሩ በእነ ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ መዝገብ ሥር ያሉ የሽብር ተከሳሾች ጉዳያቸውን በአካል እንዲከታተሉ ዛሬ ብይን ሰጠ። ሱዳን ውስጥ በተፈጸሙ የሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮኖች) ጥቃቶች ከጥር እስከ ሚያዚያ ቢያንስ 880 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን የተመድ አስታወቀ። በተመድ የአፍሪቃ ውክልና እንዲጨምር የተሀድሶ እርምጃ መውሰድ አለበት ሲሉ የተመድ ዋና ፀሀፊ አንቶንዮ ጉተሬሽ አሳሰቡ ።
We're indexing this podcast's transcripts for the first time — this can take a minute or two. We'll show results as soon as they're ready.
No matches for "" in this podcast's transcripts.
No topics indexed yet for this podcast.
Loading reviews...
ABOUT THIS SHOW
ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ ማድመጥ ትችላላችሁ። የዶይቼ ቬለ ዜና በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በየዕለቱ በቀጥታ ይደመጣል።
HOSTED BY
DW
Loading similar podcasts...