የዓለም ዜና podcast artwork

PODCAST · news

የዓለም ዜና

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ ማድመጥ ትችላላችሁ። የዶይቼ ቬለ ዜና በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በየዕለቱ በቀጥታ ይደመጣል።

Publisher-supplied feed metadata · PodParley refreshed Jun 13, 2026 · Source feed

  1. 100

    DW Amharic የነሐሴ 10 ቀን 2018 የዓለም ዜና

    የኢትዮጵያ ፌድራል መንግሥትና የትግራይ ክልል “የፖለቲካ መሪዎች የሕዝቡን ድምጽ እንዲሰሙ፣ ሰዎችን እየጎዱ ያሉ ችግሮችን የጋራ መግባባት በመፍጠር ለመፍታት እንዲሞክሩ” የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጥሪ አቀረበ። የሱዳን የሽግግር ሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀ-መንበር አብደል ፋታኅ አል-ቡርኻን በሱዳን ሊካሔድ ለታቀደው ብሔራዊ ውይይት ተሳታፊዎች “ሕጋዊ፣ ፖለቲካዊና የጸጥታ ዋስትና” ለመስጠት ቃል ገቡ። ለሊቱን በሩሲያና በዩክሬን በተፈጸሙ ኃይለኛ የድሮንና የሚሳይል ጥቃቶች በሁለቱም ሀገራት 12 ሰዎች መገደላቸውን ባለሥልጣናት አስታወቁ።

  2. 99

    የነሐሴ 9 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና

    የትግራይ እና አማራ ክልሎች በሚዋሰኑባቸው የቆቦ አካባቢዎች ዛሬ ማለዳ በኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት እና በሕወሃት ታጣቂዎች መካከል ግጭት መቀስቀሱን የአካባቢው ነዋሪዎች ለዶቼ ቬለ ተናገሩ። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ “ በመንግስት የፀጥታ አባላት ተፈጸመ “ የተባለውን ግድያ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት አወገዘ ፡፡ በኢትዮጵያ በግጭት በተጎዱ አካባቢዎች አሁንም "ከባድ" የሚባሉ ሥጋቶች መቀጠላቸውን የአውሮፓ ሕብረት ይፋ ባደረገው ኢትዮጵያን የተመለከተ የ2025 የሰብአዊ መብቶች እና የዲሞክራሲ ገጽታ ዓመታዊ ሪፖርት ላይ ይፋ ተደረገ።

  3. 98

    የነሐሴ 8 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና

    • ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ሲፒ ጄ በኢትዮጵያ በእስር ላይ የሚገኙ አምስት ጋዜጠኞች የሽብር ወንጀል ፈጽመናል ብለው አምነው ይቅርታ እንዲጠይቁ የሚደረግባቸውን ግፊት አወገዘ። • የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል በብሄራዊ ጦሩ ላይ መጠነ ሰፊ የአየር እና የምድር ጥቃት መክፈቱን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘገበ። • ዩጋንዳ በሶማሊያ የሚገኘውን የሰላም አስከባሪ ኃይሏን እዚያው እንደምታቆይ አስታወቀች። • የኢቦላ ወረርሽኝ ኮንጎ ውስጥ ተዋህሲው እስካሁን ባልደረሰበት ግዛት ውስጥ ተከሰተ • ፈረንሳይ የእስራኤል ሰፋሪዎች በኃይል በተያዘችው የዮርዳኖስ ወንዝ ዳርቻ የሚፈጽሙትን ጥቃት በይፋ አወገዘች።

  4. 97

    የሐሙስ ነሐሴ 7 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና

    አ.አ፥ ሦስት የፖለቲካ ፓርቲዎች በምክክር ሂደቱ ላይ ሥጋት እንዳላቸው ገለጡ፣ አፋር፥ ብርቱ ድርቅ ባስከተለው የውኃ እጥረት የተነሳ የቤት እንስሳት እየሞቱ ነው፣ ሞቃዲሹ፥ ሶማሊያ ውስጥ ብርቱ የረሐብ አደጋ አንዣብቧል፣ ኪየቭ፥ ዩክሬን በጦርነቱ የሚሞቱ ሰላማዊ ሰዎች በከፍተኛ ኹኔታ ጨምሯል፣ ሞስኮ፥ ዩክሬን እና ሩስያ ድንበር ዘልቀው በድሮን እየተደባደቡ ነው፣ ቦጎታ፥ በኮሎምቢያ የደረሰው ብርቱ ርእደ መሬት የነፍስ አድን ፍለጋ የመጨረሻ ደረጃ ላይ እየደረሰ ነው

  5. 96

    የነሐሴ 6 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

    የነሐሴ 6 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና በአማራ ክልል ለተፈጠረው ቀውስ ኃላፊነት ወስደው እንዲፈርሙና ከእሥር እንዲፈቱ ጥያቄ እንደቀረበላቸው የገለፁ 30 የሽብር ተከሳሾች አንፈርምም ማለታቸው ተነገረ። በአማራ ክልል በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ከፃግምና አበርገሌ ወረዳዎች ተፈናቅለው ሰቆጣ ከተማ የተጠጉ ወገኖች ለከፋ የምግብ እና የመጠለያ እጥረት ተዳርገናል እያሉ ነው። የአስተዳደር ዞኑ አደጋ ስጋትና ሥራ አመራር ኮሚሽን በበኩሉ አዲስ ለመጡት ካልሆነ ድጋፍ እየተደረገ ነው ይላል። ደቡብ አፍሪቃ ዜጎቻቸውን ወደ የሃገራቸው የመለሰችላቸው የሌሎች የአፍሪቃ ሃገራት መንግሥታት ወጪውን እንዲከፍሏት መጠየቋ ተሰማ።

  6. 95

    የነሐሴ 5 ቀን 2018 የዓለም ዜና

    -የኢትዮጵያ መንግሥት ጦር አላማጣ ከተማ አጠገብ ትምሕርት ቤት ዉስጥ የሰፈረ የትግራይ ተዋጊ ኃይልን በሰዉ አልባ አዉሮፕላን መምታቱን የትግራይ ክልል ባለሥልጣናት አስታወቁ፤ አወገዙም።በጥቃቱ ተዋጊዎችም ሰላማዊ ሰዎችም መሞት መቁሰላቸዉ ተነግሯል።---በሱዳን መከላከያ ጦር የሚመራዉ የሐገሪቱ መንግሥት «ከኢትዮጵያ የተሻገሩ» ያላቸዉ የፈጥኖ ደራሽ ኃይላት አንዲት የድንበር ከተማ ማጥቃታቸዉን አስታወቀ።- የሆርሙዝ ወሽመጥን የወደፊት አጠቃቀም በተመለከተ ኢራንና ኦማን የሚያደርጉት ድርድር የመግባባት ፍንጭ ማሳየቱን ቀጠር አስታወቀች።የዩናይትድ ስቴትስና የኢራን የስማ በለዉ ድርድርም መዛዛት መወነጃጀሉም እንደቀጠለ ነዉ።

  7. 94

    የነሐሴ 4 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

    የነሐሴ 4 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕሰተ ዜና -በምሥራቃዊ ኮንጎ የተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ የተቀሰቀሰው በግንቦት የመጀመሪያ ሣምንት ከመታወጁ ሦስት ወራት ገደማ አስቀድሞ እንደነበር የዓለም የጤና ድርጅት ዛሬ አስታወቀ። -ዩክሬን በሩስያ ላይ በጣለችው የድሮን ጥቃት ህጻናትን ጨምሮ 13 ሰዎች መገደላቸውን 39 ደግሞ መቁሰላቸውን ባለሥልጣናት ዛሬ አስታወቁ። -ኮሎምብያና ጎረቤቶቿን የላቲን አሜሪካ ሀገራት በመታው ከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ ቢያንስ 18 ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ። የርዕደ መሬት ንዝረት እስከ ኢኳዶር፣ ፓናማ እና ቬንዙዌላ ድረስ ተሰምቷል።

  8. 93

    የነሐሴ 3 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና

    • የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የኢትዮጵያ የፌዴራል መንግስቱ እና የክልል መሪዎች እውነተኛ የፖለቲካ መፍትሔ እንዲሹ ጥሪ አቀረቡ ። • በኢራን የሚደገፉት የየመን ሁቲ አማፂያን በሳውዲ አረቢያ የቀይ ባሕር ዳርቻ በሚገኘው የነዳጅ ማጣሪያ ላይ በድሮን ጥቃት ማድረሳቸውን አስታወቁ። • የሮማ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ለሚገኙ ሱዳናዉያን የሰብአዊ ርዳታ የሚያልፍባቸው መስመሮች በአስቸኳይ እንዲከፈቱ ጥሪ አቀረቡ። • አሜሪካ ኦሬገን እያስተናገደች ባለው 21ኛው የዓለም ከ20 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያዉያን አትሌቶች ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀመጡ።

  9. 92

    የነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና

    የዛሬው የዓለም ዜና በአለታ ወንዶ ከተማ በመኪና አደጋ የ7 ሰዎች ሕይወት ማለፉን፣ከ178,000 በላይ ስደተኞች ከደቡብ አፍሪቃ መልቀቃቸውን፣ኢራን እና ኦማን ስምምነት ላይ ለመድረስ ተቃርበናል ማለታቸውን፣ኢራን በኤምሬትስ መርከብ ላይ ጥቃት ፈፀመች መባሉን፣በጀርመን ወታደራዊ ጣቢያ ላይ ድሮኖች መታየታቸውን ፣እንዲሁምየአውሮፓ ህብረት የአውሮፓ ህብረት በሴውታ የተሳሳተ መረጃ ስርጭት ላይ ከትላልቅ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ጋር መምከሩን አካቷል።

  10. 91

    የነሐሴ 1 ቀን 2018 የዓለም ዜና

    -የኢትዮጵያ መንግሥት ሐገርና ሕዝብ ጎድተዋል፣ ገንዘብ አጭበርብረዋል፣ በሙስና ተዘፍቀዋል ያላቸዉን ከፍተኛ ባለሥልጣናቱን ማሰሩን አስታወቀ።----የዩጋንዳ ጦር የጋዛን ሠላም ለማስከበር ይሰፍራል ለተባለዉ ዓለም አቀፍ ሠራዊት ወታደሮች እንዲያዋጣ የሐገሪቱ ምክር ቤት ወሰነ።የጋዛን ሠላም ያስከብራል የተባለዉ ዓለም አቀፍ ሠራዊት የሚሰፍርበት ጊዜ በዉል እይታወቅም።--ሳዑዲ አረቢያ፣ ቱርክና ፓኪስታን የጦር ቃል ኪዳን ሥምምነት ተፈራረሙ።የሶስቱ ሐገራት መሪዎች ዛሬ መካ-ሳዑዲ አረቢያ ዉስጥ በተፈራረሙት ሥምምነት መሠረት አንዱ ሐገር ከተጠቃ ሶስቱም እንደተጠቁ ይቆጠራል።

  11. 90

    የሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

    የሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና የኢትዮጵያ መንግሥት ጦርና ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ታጣቂዎች ለተጨማሪ ዉጊያ የሚያደርጉት ዝግጅት መቀጠሉን የተለያዩ ወገኖች አስታወቁ። ከራያ አለማጣና አካባቢው በጦርነት ስጋት ከተፈናቀሉ ሴቶች መካከል በርካቶቹ ለአሰቃቂ የቡድን ጾታዊ ጥቃት፣ ለአካል ጉዳትና ለሕክምና እጦት ችግር መዳረጋቸውን አስታወቁ። የህክምና ባለሞያ ለጥቃት ተጋላጭ ለሆኑት ሴቶች ከለላ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል። የአዲስ ስታንዳርድ ባለቤት Jakenn Publishing Plc እንዳስታወቀዉ ዋና አዘጋጅ ዮናስ ከድር በመንግሥት የሥለላ ኃይላት ከመታገቱ በተጨማሪ ተደብድቧል፤ ተንገላትቷል፤ ታስሯልም።

  12. 89

    የሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

    በጋምቤላ ክልል ኑዌር ብሔረሰብ ዞን በሚገኙ አምስት ወረዳዎች የተከሰተው የዝናብ እጥረት የተለያዩ ሰብሎችና አትክልቶችን ለጉዳት መዳረጉን ነዋሪዎች እና የዞኑ አስተዳደር ለዶቼቬለ ተናገሩ። በዴሞክራቲክ ኮንጎ ምሥራቃዊ ግዛት የተቀሰቀሰው የኢቦላ ተሐዋሲ ስርጭት መባባሱ ተገለጸ። የሟቾች ቁጥር ከ1,700 በልጧል። በኢራን የሚደገፉት የሁቲ አማጽያን በአንድ ተጨማሪ የሳዑዲ አረብያ ነዳጅ ጫኝ መርከብ ላይ ጥቃት መፈጸመቸው ተዘገበ። ሩሲያ በዩክሬን ዋና ከተማ ኪየቭና አካባቢው ላይ በሚሳኤል እና በሰው አልባ አውሮፕላኖች ባደረሰችው ጥቃት ቢያንስ 17 ሰዎች ተገደሉ፤ ከ40 በላይም ቆሰሉ።

  13. 88

    የሐምሌ 28 ቀን 2018 የዓለም ዜና

    -ሱዳንን ከኢትዮጵያ ጋር በሚያዋስነዉ የሴቲት ወንዝ ዉስጥ 15 የትግራይ ተዋጊዎች አስከሬን መገኘቱን የሱዳን የሕክምና ባለሙያዎች አስታወቁ።የኢትዮጵያ መንግሥት ጦርና የህወሓት ተዋጊዎች አዲስ የገጠሙት ዉጊያና የዉጊያ ዝግጅት ሰላማዊ ሰዎችን ለከፋ አደጋ እንደሚያጋልጥ አምንስቲ ኢንተርናሽናል አስጠነቀቀ።-ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን የሚያደርጉት ድርድር አግባቢ ዉጤት እያሳየ መሆኑን አደራዳሪዎችና የአሜሪካ ባለሥልጣናት አስታወቁ።-የእስራኤል ጦር የዛሬ ሶስት ዓመት ግድም ጋዛ ከተማ ዉስጥ በጅምላ የገደላቸዉ 112 ፍልስጤማዉያን ዛሬ በጅምላ ተቀበሩ።

  14. 87

    የሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

    የሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ-ዜና በራያ አላማጣ ግንባር ወታደራዊ ፍጥጫ እና የጦርነት ዝግጅት ማየሉን ነዋሪዎች ገለጹ። በአካባቢው ፣ ቤት ለቤት ዝርፊያ መስፋፋቱን የትራንስፖርትና የባንክ አገልግሎት በመስተጓጐሉ ደንበኞች ለተጨማሪ ክፍያ መዳረጋቸውንም ተናግረዋል በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ጦርነት ሸሽተው ከትግራይ ክልል ወደ ሱዳን እየገቡ ነው ሲል ኤ ኤፍ ፒ ዘገበ። ከመካከላቸው ቁስለኛ ተዋጊዎች ይገኙበታል የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚካሄደውን ጦርነት ከፍጻሜ ለማድረስ ዛሬ ሰኞ ድርድር ይጀመራል ሲሉ ቴህራን ደግሞ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ድርድር እያካሄድኩ አይደለም ብላለች

  15. 86

    የሐምሌ 26 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና

    በመከላከያ ሠራዊትና በትግራይ የጸጥታ ኃይሎች መካከል ሸረሪና በተባለ ቦታ የተጀመረው ውጊያ መቆሙን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘገበ። እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ፈጸመችው በተባለ የአየር ጥቃት 15 ፍልስጤማውያን ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን የጋዛ ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ጦርነቱን ለማስቆም በአፋጣኝ ስምምነት ላይ ከተደረሰ ዩናይትድ ስቴትስና እስራኤል በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት ላለመሰንዘር መስማማታቸውን ገለጹ። በኢንዶኔዥያ በአንዲት ጀልባ በደረሰ የእሳት አደጋ 5 ተሳፋሪዎች ሞተው 41 የደረሱበት አለመታወቁን የሐገሪቱ ባለስልጣናት አስታወቁ።

  16. 85

    የሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና

    የዛሬው የዓለም ዜና ፤በትግራይ አዲስ ጦርነት መከፈቱን የትግራይ ቴሌቪዥን መዘገቡን፣በሲውታ፤ ስፔን እና ሞሮኮ የድንበር በተከሰተው የስደተኞች ቀውስ የሟቾች ቁጥር 67መድረሱን፣በስፔኗ ሲኡታ ግዛት የሚፈልሱ ስደተኞችን በተመለከተ ውይይት እንዲደረግ የአውሮፓ ህብረት ሀገራት ጥሪ ማቅረባቸውን፣ሁቲዎች የሳውዲ የነዳጅ ጫኝ መርከቦች የጉዞ መስመር እንዲቀይሩ ማድረጋቸውን፣እስራኤል በፈፀመችው ጥቃት በጋዛ ሁለት ሰዎች ሲገደሉ የመድኃኒት ማከማቻ መጋዘኖችን መውደማቸው መገለፁን እንዲሁም ኢራን አሜሪካን እንዳያግዙ የአካባቢውን መንግስታትን ማስጠንቀቋን አካቷል።

  17. 84

    የሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና

    የዛሬው የዓለም ዜና ፤በትግራይ አዲስ ጦርነት መከፈቱን የትግራይ ቴሌቪዥን መዘገቡን፣በሲውታ፤ ስፔን እና ሞሮኮ የድንበር በተከሰተው የስደተኞች ቀውስ የሟቾች ቁጥር 67መድረሱን፣በስፔኗ ሲኡታ ግዛት የሚፈልሱ ስደተኞችን በተመለከተ ውይይት እንዲደረግ የአውሮፓ ህብረት ሀገራት ጥሪ ማቅረባቸውን፣ሁቲዎች የሳውዲ የነዳጅ ጫኝ መርከቦች የጉዞ መስመር እንዲቀይሩ ማድረጋቸውን፣እስራኤል በፈፀመችው ጥቃት በጋዛ ሁለት ሰዎች ሲገደሉ የመድኃኒት ማከማቻ መጋዘኖችን መውደማቸው መገለፁን እንዲሁም ኢራን አሜሪካን እንዳያግዙ የአካባቢውን መንግስታትን ማስጠንቀቋን አካቷል።

  18. 83

    የሐምሌ 24 ቀን 2018 የዓለም ዜና

    -የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሐን ባለሥልጣን «የይዘት ግዴታዎችን ተላልፈዋል» ላላቸዉ ለሁለት የሐገር ዉስጥ ማሰራጪያ ጣቢያዎች «የመጨረሻ« ያለዉን የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ሰጠ። ማስጠንቀቂያዉ የተሰጣቸዉ አሐዱ ኤፍ ኤም 94.3ና አርትስ ቴሌቪዥን ጣቢዎችን ባለሥልጣኑ «ያልተረጋገጠ፣ ሚዛናዊ ያልሆነና የሕዝብ ጥቅም የሚጎዱ» ያላቸዉን መረጃዎች አሰራጭተዋል በማለት ወቅሷልም።-ሶማሊያ ዉስጥ ለሰፈረዉ የአፍሪቃ ሕብረት ሠራዊት ወታደሮች ያዋጡ ሐገራት መሪዎች ዛሬ ሲነጋገሩ ዋሉ።--ከ60 ሺሕ የሚበልጡ ስደተኞች ባጭር ጊዜ ዉስጥ የስጳኝን ግዛት ሴኡታን ማጥለቅለቃቸዉ ለስጳኝና ለሞሮኮ አስደንጭ፣ ለተቀሩት የአዉሮጳ ሐገራት አሳሳቢ ሆኗል።

  19. 82

    የሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና

    • የኢትዮጵያ የፌደራል ፖሊስ ከማላዊ ፖሊስና ከኢንተርፖል ጋር በመተባበር በኢትዮጵያዉን ወጣቶች ላይ «ከባድ ኢሰብአዊ ድርጊት ሲፈጽም ነበር» ያለዉን ተጠርጣሪ መያዙን አስታወቀ። • በሱዳን ሰሜን ኮርዶፋን ግዛት በተፈጸመ የድሮን ጥቃት ዘጠኝ ሰቪሎች መገደላቸውን የሕክምና ምንጮች ገለጹ። • በግብፅ ዳሚየታ ወደብ ላይ የደረሰው ቃጠሎ የድሮን ጥቃትን ተከትሎ የተነሳ መሆኑን የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ዐስታወቀ። • ሩሲያ በዩክሬን ላይ ባካሄደችው ከፍተኛ የ ሚሳኤል እና የድሮን ጥቃት ሕፃናትን ጨምሮ ቢያንስ ስምንት ሰዎች ተገደሉ።

  20. 81

    የሐምሌ 22 ቀን 2018 የዓለም ዜና

    -ሳዑዲ አረቢያ «ሐሺሽ ይዘዉ ተገኝተዋል» በሚል የወነጀለቻቸዉን አምስት ኢትዮጵያዉያን ሥደተኞችን በሞት ቀጣች።ሑዩማን ራይትስ ዋች እንዳስታወቀዉ ሳዑዲ አረቢያ የግሪጎሪያኑ 2026 ከባተ ካለፈዉ ጥር ወዲሕ በተመሳሳይ ወንጀል ተሳትፈዋል ያለቻቸዉን 17 ኢትዮጵያዉያንን ያለ ተገቢ የፍርድ ሒደት በሞት ቀጥታለች።----የተለያዩ የወንጀል መረቦች «ሥራ ታገኛላችሁ» በሚል ከየሐገሩ እያስኮበለሉ በየማጭበርበሪያ ማዕከላቱ የሚሰቃዩና የሚያሰሯቸዉ ሰዎች ብዛት በመቶ ሺሕ ሊቆጠር እንደሚችል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታወቀ።---ዩናይትድ ስቴትስ ከኢራን ጋር በገጠመችዉ ጦርነት ሳዑዲ አረቢያም ቀስ በቀስ እየተዘፈቀችበት ነዉ።

  21. 80

    የዓለም ዜና፤ ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ማክሰኞ

    አርስተ ዜና፤ አዲስ አበባ ላይ ለሁለት ቀናት የሚዘልቀው 49ኛው የአፍሪቃ ኀብረት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉባዔ፣ አህጉሪቱን ለገጠሟት የፀጥታ ችግሮች ትኩረት መስጠት እንዳለበት ተነገረ። -መቀመጫቸዉን ቤንጋዚ የያደረጉ የሊቢያ ባለሥልጣናት፣ የተለያዩ ዜግነት ያላቸውን ቢያንስ 117,350 ሕገ-ወጥ ያሏቸውን ስደተኞች ከአገር ማባረራቸዉን ገለፁ። በሌላ በኩል ከ100,000 የሚበልጡ ፈቃደኛ ሱዳናውያን ወደ አገራቸው ለመመለስ ተመዝግበዋል።-ጠ/ሚቤንያሚን ኔታንያሁና የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ በሟቹ የአሜሪካ የምክር ቤት አባል የሐዘን ሥነ ሥርዓት ላይ ለመገኘት ዋሽንግተን ገቡ።

  22. 79

    የሐምሌ 20 ቀን፤ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና

    የዛሬው የዓለም ዜና ፤በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ አርሲ ከ450 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ኢሰመጉ ይፋ ማድረጉን፣የናይጄሪያ ጦር በታጣቂ ቡድን የተጠለፉ 48 ሰላማዊ ሰዎችን በዘመቻ ማስለቀቁን፣በኢራን የሚደገፉት የየመን የሁቲ አማፂያን በሳዑዲ አረቢያ የነዳጅ መሠረተ ልማት ላይ የድሮን ጥቃቶች መጀመራቸውን፣የጀርመን መራሄ መንግስት ፍሬድሪሽ ሜርዝ ቅዳሜ በበርሊን በተፈፀመው ጥቃት ምላሽ እንዲሰጥ ጥሪ ማቅረባቸውን ፣ኢራን ከአሜሪካ ጋር ምንም አይነት ድርድር ውስጥ እንዳልሆነች መግለጿን እንዲሁም በአሜሪካ ሲያትል በተካሄደ የምግብ ፌስቲቫል በተኩስ ልውውጥ ቢያንስ ሶስት ሰዎች መገደላቸውን አካቷል።

  23. 78

    የሐምሌ 19 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና

    የዛሬው የዓለም ዜና ፤ከባድ የአየር ንብረት መዛባት የሚያስከትለው «ሱፐር ኤል ኒኖ» በአፍሪካ ሃገራት ላይ ከ10 እስከ 20 ቢሊዮን ዶላር የሚሆን የኢኮኖሚ ጉዳት ያደርሳል መባሉን፣በበርሊን የተፈፀመው ጥቃት ከሽብር ጋር የሚይያያዝ ነው ሲል የጀርመን ፖሊስ መግለፁን፣በፈረንሳይ ሰደድ እሳት 250,000 በላይ ሰዎችን ማፈናቀሉን እንዲሁም ብራዚል ከምርጫ በፊት የአሜሪካ ባለስልጣናት ወደ ሀገሯ እንዳይገቡ መከልከሏን አካቷል።

  24. 77

    የሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና

    • በኮንጎ በኤቦላ ቫይረስ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር ከ3000 ማለፉ በተሰማበት በዛሬው ዕለት (ቅዳሜ) የጤና ባለሞያዎች የስራ ማቆም አድማ አደረጉ ። • የየመኑ ሁቲ አማፅያን በሳዑዲ አረቢያ ግዙፍ የነዳጅ ማጣሪያ ተቋማት ላይ የድሮን እና የሚሳኤል ጥቃት መፈጸማቸውን አስታወቁ። • ሩስያ እና ዩክሬን አንዳቸው በሌላው ላይ በደረሷቸው የድሮን እና የሚሳኤል ጥቃቶች ከበርካታ ሰዎች ተገደሉ። • በደቡባዊ ምዕራብ ፈረንሳይ የተቀሰቀሰው የሰደድ እሳት በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋ መምጣቱን ተከትሎ ባለስልጣናት ነዋሪዎችን ከአካባቢው ማስለቀቅ ጀመሩ።

  25. 76

    የዕለተ ዐርብ ሐምሌ 17 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና

    የአፍሪቃ ኅብረት በቀይ ባሕር የተፈፀመውን የመርከቦች ጥቃት አወገዘ፤ ጋሮዌ፥ የአደን ባሕረ ሠላጤ የየመን ክልል ላይ የታገተችው የንግድ መርከብ በሶማሌ የባሕር ላይ ወሮበሎች ቁጥጥር ስር ናት፤ ኪንሻሳ፥ የዘንድሮው የኢቦላ ወረርሺኝ ከከዚህ ቀደሙ በሦስት እጥፍ የተፋጠነ ነው፤ ቤርሊን፥ የጀርመን መንግሥት የካቢኔ አባላት ለውጥ አደረ፤ ማድሪድ፦ በዐሥር ሺህዎች የሰደድ እሳት ፍራቻ ተፈናቅለዋል፤ ቤርሊን፥ ዬርገን ክሎፕ የጀርመን ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ኾኑ

  26. 75

    የሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

    የሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ቦረና ወረዳ በሚገኘው አባይ ገዳመ አስቄጤስ አቡነ አረጋዊ እና ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም ላይ ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ተፈፀመ በተባለ የድሮን ጥቃት የ2 መነኮሳት ህይወት ማለፉን የገዳሙ አበምኔትና የወረዳዉ ቤተክህነት ኃላፊ ተናገሩ። በኢራን የሚደገፉት የሁቲ አማጽያን ዛሬ ቀይ ባህር ላይ በነበሩ ሁለት የሳዑዲ አረብያ ነዳጅ ጫኝ መርከቦች ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን ተናግረዋል። ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን ትናንት የተፈራረሙት ስምምነት ሳዑዲ አረብያ ከእስራኤል ጋር መደበኛ ግንኙነት እንዲኖራት የሚጠይቅ መሆኑን ትራምፕ አስታወቁ።

  27. 74

    የሐምሌ 15 ቀን 2018 የዓለም ዜና

    -የኢትዮጵያ የፌደራል ፖሊስ «አደገኛ የሰዉ አዘዋዋሪ ወንጀለኛ» ያለዉን 17 አባላት ያሉት መረብን መበጣጠሱን አስታወቀ።---የዓለም የረሐብተኞች ቁጥር አምና ለሶስተኛ ተከታታይ ዓመት መቀነሱን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታወቀ።የረሐብተኛዉ ቁጥር ቢቀንስም የዓየር ንብረት መዛባትና የንግድ መደናቀፍ የረሐብተኛዉን ቁጥር እንደገና ሊያንረዉ ይችላል።-ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን የገጠሙት ጦርነት የባብ ኤል መንደብን መስመርም አዘግቷል።የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ ተፋላሚዎች የሲቢል ተቋማትን እንዳይመቱ ተማፅነዋል።የአሜሪካ ፕሬዝደንት ግን የኢራንን ድልድዮችና የነዳጅ ተቋማት ለማዉደም እየዛቱ ነዉ።

  28. 73

    የዓለም ዜና፤ ሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ማክሰኞ

    አርስተ ዜና፤ ኢሕአፓ በትግራይ አዲስ የጦርነት ሥጋት ማንዣበቡን በመግለፅ ጥሪ አቀረበ። ፓርቲው መንግሥት በሚያስተዳድራቸው መገናኛ ብዙኃን የሚካሄድ ያለው "የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ እና የሕዝብን ሥነ-ልቦና ለጦርነት የማዘጋጀት ሙከራ" ከአራት ዓመታት በፊት በትግራይ ጦርነት ዋዜማ ከታየው ሂደት ጋር አንድ አይነት ነው"ብሏል።- የአራት ቀናት አፍሪቃ ሃገራት ጉብኝታቸዉን ከሞሪታንያ የጀመሩት የጀርመኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዮሃን ቫዴፉል የሞሪታንያ ጉብኝታቸዉን አጠናቀዉ ናይጀርያ ገብተዋል። ሚኒስትሩ አገራቸዉ እና ሞሪታኒያ በንግድ፣ በኃይል ቀርቦትና በደኅንነት ዘርፎች ላይ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ እንደሚያጠነክሩ ገልፀዋል።

  29. 72

    የሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

    የሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና ከሱዳኑ ፈጥኖ ደራሹ ኃይል ጋር በምታካሂደው ጦርነት ኬሚካዊ የጦር መሣሪያዎችን ጥቅም ላይ አውላለች ባለቻት በሱዳን ላይ ዩናይትድ ስቴትስ ዛሬ አዲስ ማዕቀብ ጣለች።ለክሱ ያቀረበችው ማስረጃ ግን የለም ተብሏል። ዛሬ የተመረጡት አዲሱ የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንዲ በርንሀም መንግሥት እንዲመሰርቱ በንጉሥ ቻርልስ ሣልሳዊ ተጠየቁ። የቀድሞ የግሬተር ማንቼስተር ከንቲባ የ56 ዓመቱ በርንሀም ጠቅላይ ሚኒስትር የሆኑት የሌበር ፓርቲ መሪነት ከተመረጡ ከ3 ቀናት በኋላ ነው። የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ አሸናፊ የስፔን ቡድን ዛሬ ወደ ሀገሩ ሲመለስ የጀግና አቀባበል ተደርገለት።

  30. 71

    DW Amharic የሐምሌ 12 ቀን 2018 የዓለም ዜና

    በሶማሌ ክልል ቀብሪ በያሕ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ12 ሰዎች ሕይወት አለፈ። ለ2019 የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት 704 ቢሊዮን ብር በጀት አጸደቀ። በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ምዕራባዊ ክፍሎች፤ በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልልና በጋምቤላ ክልል በተወሰኑ አካባቢዎች በሚጥል ከባድ ዝናብ ምክንያት የጎርፍ መጥለቅለቅ ሊከሰት እንደሚችል የኢትዮጵያ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስጠነቀቀ። የታንዛኒያ ሰንደቅ የሚያውለበልብ ነዳጅ ጫኝ መርከብ ከየመን የባሕር ዳርቻ በሶማሊያ የባሕር ላይ ወንበዴዎች ታገተ። አሜሪካ ሁለት ወታደሮቿ በዮርዳኖስ ከተገደሉ በኋላ ኢራንን “ለመቅጣት” አዲስ ዙር የለሊት የአየር ላይ ድብደባ ፈጸመች።

  31. 70

    የሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ-ም የዓለም ዜና

    የዛሬው የዓለም ዜና ፤በአዲስ አበባ ከተማ ህወሓትን የሚቃወም ሰልፍ መካሄዱን፤ኢራን 'የአሜሪካ ጥቃቶች ከቀጠሉ ምንም አይነት የፖለቲካ ድንበር ደህንነቱ የተጠበቀ አይሆንም' ስትል ማስጠንቀቋን፣የሊባኖስ ፕሬዝዳንት ትራምፕን ለማግኘት ወደ ዋሽንግተን ማቅናታቸውን፤በጀርመን ከፍተኛ የሽብር ስጋት መኖሩን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር መግለፁን፣ዩክሬይን በሁለት የሩስያ ግዛቶች ሌሊቱን ለዛሬ አጥቢያ ፈጸመችው በተባለ የድሮን ጥቃቶች 9 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን የሩስያ ባለስላጣናት ማስታወቃቸውን እንዲሁም ህንድ የመጀመሪያውን የግል ሮኬት ወደ ህዋ ማምጠቋን አካቷል።

  32. 69

    የሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና

    በዛሬው የዓለም ዜና፤ የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂና የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀ-መንበር አብደል ፋታኅ አል ቡርኻን በአስመራ መገናኘታቸውን፣ሶማሊያ በየኮቪድ-19 ሰበብ የ250 ሚሊዮን ዶላር ማጭበርበር የተከሰሰ ቁልፍ ተጠርጣሪን ለአሜሪካ አሳልፋ መስጠቷን፣የኢራን አብዮታዊ ዘብ በዮርዳኖስ የአሜሪካን አውሮፕላኖችን በሚሳኤልና በድሮን መምታቱን፣ አንዲ ቡርንኻም በብሪታኒያ በሥልጣን ላይ የሚገኘው ሊበር ፓርቲ መሪ ሆነው መመረጣቸውን እና ቻይና አሜሪካ በጋዜጠኞች የቆይታ ጊዜ ላይ በጣለችው ገደብ ላይ 'የአፀፋ እርምጃዎችን' እንደምትወስድ ማስጠንቀቋን አካቷል።

  33. 68

    የሐሙስ ሐምሌ 9 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና

    አ.አ፥ ስለተጀመረው አገራዊ ምክክር የፓርቲዎች ትችት እና ድጋፍ፤ ሙዋንጋ ፥ ዛምቤዚ ባህር ሰጥመዋል የተባሉ ኢትዮጵያዉያን በሕይወት ተገኙ፤ ዋሽንግቶን፥ ዩናይትድ ስቴትስ በኢቦላ ከተጠቃችው ኮንጎ የሚመጡ ዜጎቿን ወደ አገር መግባት ከለከለች፤ ኪዬቭ፥ አዲስ ጠቅላይ ሚንሥትት ተሾሙ፥ መከላከያ ሚንሥትሩ ተሻሩ፤ቴሕራን፥ ኢራን ዩናይትድ ስቴትስ ስትደበድባት የባህረ ሠላጤው አገራት ላይ ጥቃቷን አጠናከረች፤ ሣንዓ፥ የሑቲ ዓማጺያን የሣዑዲ ዓረቢያን እንደሚደበድቡ ዛቱ

  34. 67

    የሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

    የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ ተጀምሯል። ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ « ለእኔ ሳይሆን ለእኛ፣ ለኢትዮጵያ ማለት ከቻልን ምክክሩ ፍሬያማ ይሆናል በማለት ለጉባኤተኞቹ ጥሪ አቅርበዋል። ወደቦትስዋና ለመሻገር የሞከሩ 10 ኢትዮጵያውያን የተሳፈሩባት ታንኳ ተገልብጣ ሳይሰጥሙ እንዳልቀረ የዛምብያ ባለሥልጣናት ዛሬ አስታወቁ። በታንኳዋ ተሳፍረው ከነበሩት 15 ኢትዮጵያውያን አስሩ ሰጥመዋል ተብሎ እንደሚታመን የተናገረው ፖሊስ ሦስት ደግሞ የደረሱበት እንዳልታወቀ ገልጿል። ከመካከላቸው በህይወት የተረፉትን ሁለቱን ፖሊስ አስሯቸዋል። የዩናይትድ ስቴትስ እና የኢራን ጥቃትና የአጸፋ ጥቃት ዛሬም ቀጥሏል።

  35. 66

    የዓለም ዜና፤ ሐምሌ 7 ቀን 2028 ዓ.ም ማክሰኞ

    አርስተ ዜና-የአሜሪካ ጦር ለሦስተኛ ተከታታይ ምሽት በኢራን ኢላማዎች ላይ ጥቃቶችን ማካሄዱን አስታወቀ። የኢራን አብዮታዊ ዘብ በበኩሉ ፤ በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ሁለት ከፍተኛ ነዳጅ መርከቦችን መምታቱን እና ከጉዞ ማሰናከሉን አስታውቋል።-ከስድስት ዓመት በላይ ከኦሮሚያ ክልልና ሌሎች አካባቢዎች ተፈናቅለው በአማራ ክልል ሰሜንና ደቡብ ወሎ ዞን በመጠለያ ጣቢያና ከማህበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው የሚኖሩ ከ60 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ለከፍተኛ የምግብ ዋስትና ሥጋት መጋለጣቸውን ተናገሩ።-አውሮጳ ህብረት በሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት ላይ የሚዉለዉን የገንዘብ ድጋፍ ለመቀነስ በሱዳን የወርቅ ንግድ ላይ አዲስ ማዕቀብ ጣለ።

  36. 65

    የሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና

    የኢትዮጵያ የፌደራል መንግስት በትግራይ ክልል እየተፈጸመ ያለውን የሰብአዊ መብቶች ጥሰት በአስቸኳይ በማስቆም ሕገ መንግስታዊ ግዴታውን እንዲወጣ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) አሳሰበ። የየመን ሑቲ ታጣቂዎች ሳውዲ ዓረብያ በሰነዓ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ«ፈጸመችው» ላሉት ጥቃት አጸፋዊ ምላሽ እንደሚሰጡ አስጠነቀቁ። አሜሪካ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ በሆርሙዝ ሰርጥ «እየፈጸመው ነው» ላለችው ማስተጓጎል ያስታገሰ ያለችውን ጥቃት መፈጸሟን አስታወቀች። ኢራን በበኩሏ በዮርዳኖስ፣ ባሕረይና ኩዌት የሚገኙ የአሜሪካ ጦር ሰፈሮችን ደብድባለች።

  37. 64

    የሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና

    • የሱዳን ፍርድ ቤት መሐመድ ሐምዳን ዳግሎን ጨምሮ 16 የፈጥኖ ደራሹ ኃይል RSF አመራር በሌሉበት የሞት ቅጣት ፈረደ። • ደቡብ አፍሪካ ሶስት የቤተሰቡን አባላት በመግደል ሸሽቶ ወደ ሐገሯ ገብቶ የነበረውን ብሪታንያዊ አሳልፋ ልትሰጥ ነው። • የኢራን አብዮታዊ ዘብ የሆርሙዝ ሰርጥ መዝጋቱን አስታወቀ። • የእስራኤል ጦር ኃይል በጋዛ ሰርጥ ባደረሳቸው ጥቃቶች አንዲት የ9 ዓመት ሴት ልጅን ጨምሮ ሶስት ሰዎች መገደላቸውን የፍልስጤም የጤና ባለስልጣናት አስታወቁ። • የቀድሞው የቃጣር መሪ ሼክ ሐማድ ቢን ኻሊፋ አል ታኒ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ ። 74 ዓመታቸው ነበር ።

  38. 63

    DW Amharic የሐምሌ 04 ቀን 2018 የዓለም ዜና

    አሜሪካ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ለስድስት አገራት ዜጎች የተሰጠውን በአገሪቱ የመቆየትና የመሥራት ጊዜያዊ ከለላ ለተጨማሪ ቀናት አራዘመች። የሱዳን ብሔራዊ ጦር አሜሪካ ያዘጋጀችውን ምክረ-ሐሳብ የሚቀበለው ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ከተቆጣጠራቸው ከተሞች ለቅቆ ሲወጣ እንደሆነ ቅድመ-ሁኔታ አስቀመጠ። የናይጄሪያ ጦር በዛምፋራ ከ300 በላይ ታጣቂዎች ገደለ ተባለ። የኢራን መንፈሳዊ መሪ ሞሽታባ ኻሜኒ አገራቸው የአባታቸውን ገዳዮች መበቀሏ “አይቀሬ” እንደሆነ ዛቱ። የአሜሪካው ፕሬዝደንት በኢራን ላይ ያነጣጠሩ 1,000 ሚሳይሎች መጠመዳቸውን አስጠንቅቀዋል። ሩሲያ በዩክሬን ላይ በፈጸመቻቸው ጥቃቶች ስድስት ሰዎች ሲገደሉ 29 ቆሰሉ።

  39. 62

    የሐምሌ 3 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

    የሐምሌ 3 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና ከዩናይትድ ስቴትስ ወደ ኢኩዋቶርያል ጊኒ የተጠረዙ ከኢትጵዮያ፣ከአንጎላ እና ከሞሪቴንያ መሆናቸው የተገለፀ 17 ስደተኞች በተያዙበት ሆቴል ውስጥ በኤቦላ እንደተያዘ የሚጠረጠር ቢያንስ አንድ ሰው ተገልሎ እንደሚገኝ የተጠራዦቹ ጠበቆች ተናገሩ። ማላዊ 38 ሺህ ዜጎቿን በአንድ ወር ውስጥ ከደቡብ አፍሪቃ ወደ ሀገራቸው መመለሷን ዛሬ አስታውቃለች። ስድስት የማላዊ ዜጎች መንገድ ላይ ታመው ሞተዋል። የጀርመን የእግር ኳስ ፌደሬሽን በምህጻሩ DFB ፕሬዝዳንት እና ምክትላቸው ለጀርመን ብሔራዊ ቡድን አስልጣኝነት ከታጩት ከዩርገን ክሎፕ ጋር ለመነጋገር ዛሬ ወደ ኒውዮርክ ተጓዙ።

  40. 61

    የሐሙስ ሐምሌ 2 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና

    ናሜይ፥ ሩስያ እና የሣኅል ቀጠና አገራት ወታደራዊ ግንኙነታቸውን ሊያጠናክሩ ነው ፤ አንካራ፥ የኔቶ ጉባኤ በተሳታፊዎች ስምምነት ተጠናቀቀ፤ቤርሊን፥ ራኄ መንግሥት ፍሪደሪሽ ሜርስ ትናንት የተጠናቀቀው ኔቶ ጉባኤ ከጠበቁት በላይ መኾኑን ተናገሩ፤ ቴሕራን፥ ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በመካከለኛው ምሥራቅ ጥቃት እየተሰናዘሩ ነው፤ ማሽሐድ፥የቀድሞዉ የኢራን ላዕላይ መሪ አያቶላሕ ዓሊ ኻምኔይ ተቀበሩ፤ ሞሮኮ እና ፈረንሣይ ወደ ግማሽ ፍጻሜ ለማለፍ ፍልሚያ

  41. 60

    የዓለም ዜና፤ ሐምሌ 01 ቀን 2018 ዓም ረቡዕ

    አርስተ ዜና፤ የደቡብ አፍሪቃ ፖሊስና ወታደራዊ ኃይል በጆሃንስበርግ አቅራቢያ በሕገ-ወጥ የማዕድን ቁፋሮ ሥራዎች ላይ ባደረጉት ከፍተኛ ዘመቻ ከ200 በላይ ሰዎችን አሰሩ። በደቡብ አፍሪቃ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን መካከል ህጋዊ ወረቅት የሌላቸዉ ስለመያዝ አለመያዛቸዉ እስካሁን የወጣ ግልፅ መረጃ የለም።-የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኔቶ ስብሰባ አንካራ ተገኝተዋል። ትራምፕ ድርጅቱ ባሳየዉን ወታደራዊ ኤግዚቢሽን የተደሰቱ አይመስልም። የአውሮጳ ህብረት ሀገራት ኔቶን ለማጠናከር የሚያደርጉትን ጥረትና የኢራን ጦርነት ለመቀላቀል ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ትራምፕ በተደጋጋሚ ተችተዋል።

  42. 59

    የማክሰኞ ሰኔ 30 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና

    አ.አ፥ ጠ/ሚ ዐቢይ ስለ ሕገ መንግሥቱ ተናገሩ፤ ናይሮቢ፥ የኬንያ ፖሊስ የመታሰቢያ ሰልፍ ከለከለ፤ ​​​​​​​ኪንሻሳ፥ የኢቦላ ወረርሺኝ በኮንጎ መዛመቱን እንደቀጠለ ነው፤ ደማስቆስ፥ ሶሪያ ውስጥ በፈረንሣይ ፕሬዚደንት ጉብኝት ወቅት በደረሰ ፍንዳታ 18 ሰዎች ቆሰሉ፤ ፓሪስ፥ ፈረንሣይ እና ሶሪያ በጋራ ለመሥራት ተስማሙ፤ አትላንታ፥ ወደ ሩብ ፍጻሜ ለመግባት የመጨረሺያ ግጥሚያዎች

  43. 58

    DW Amharic የሰኔ 29 ቀን 2018 የዓለም ዜና

    የትግራይ ክልል ባለሥልጣናት የ15 ዓመት አዳጊዎችን ጨምሮ ሲቪል ሰዎችን እያፈኑ በግዳጅ ለውትድርና በመመልመል ላይ እንደሚገኙ ሒውማን ራይት ዎች ወነጀለ። በሱዳን እየተካሔደ በሚገኘው ጦርነት በስድስት ወራት ብቻ 330 ሕጻናት መገደላቸውን የተባበሩት መንግሥታት የሕጻናት መርጃ ድርጅት አስታወቀ። ሐማስ የጋዛን መንግሥታዊ መዋቅር መፍረሱን አስታወቀ። የዩክሬን ጦር ኦምስክ በተባለ ግዙፉ የሩሲያ የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ጥቃት ፈጸመ። ለጀርመን ለሚቀጥለው ዓመት የ555.4 ቢሊዮን ዩሮ ረቂቅ በጀት ጸደቀ። ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ ከኢራን ጋር ከሥምምነት ላይ ካልደረሰች አገራቸው የጀመረችውን ጦርነት "እንጨርሰዋለን" ሲሉ ዛቱ

  44. 57

    DW Amharic-የሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም፤ የዓለም ዜና

    በዛሬው የዓለም ዜና በቀይ ባሕር ትቀዝፍ የነበረች አንዲት ዕቃ ጫኝ መርከብ በየመን ሁዴይዳ የባሕር ክልል አካባቢ ጥቃት ተፈፀመባት መባሉን፣ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ በሂዝቦላህ ላይ የምታካሂደውን ዘመቻ አጠናክራ እንደምትቀጥል መግለጿን፣በእስራኤል እስር ቤት ውስጥ የሚገኙት የጋዛ ሆስፒታል ዳይሬክተር ህይወታቸው አደጋ ላይ ወድቋል መባሉን፣ ሁለተኛ ቀኑን በያዘው የአያቶላህ አሊ ካማኔይ የሀዘን ሥነ ሥርዓት ላይ ልጆቻቸው እና ከፍተኛ የኢራን ባለስልጣናት መገኘታቸውን እንዲሁም ትራምፕ በአሜሪካ 250ኛ ዓመት የነፃነት በዓል ባደረጉት ንግግር የሀገር ፍቅርን ከፓርቲ ፖለቲካ ጋር ቀላቅለዋል በሚል መተቸታቸውን አካቷል።

  45. 56

    የሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም፤ የዓለም ዜና

    በዛሬው የዓለም ዜና ፤ የትግራይ ክልል አሁን ያለበት ሁኔታ አሳስቦኛል ሲል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን መግለፁን፣የአውሮፓ እና የአሜሪካ መሪዎች ስደተኞችን ለመጠበቅ እና ለማዋሃድ የበለጠ እንዲሰሩ የሮማ ካቶሊክ ሊቀ ጳጳሥ ማሳሰባቸውን፣ኢራን ለሟቹ መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አሊካሜኒ ብሄራዊ የሽኝት ሥነ ስርዓት ዛሬ በይፋ መጀመሯን፣ጀርመን፤ ቤጂንግ የሩሲያ ወታደሮችን ማሰልጠኗን የሚያሳዩ ዘገባዎች መውጣታቸውን ተከትሎ ቻይናን ማስጠንቀቋን፣አማራጭ ለጀርመን የተባለው መጤ ጠል ፓርቲ ዛሬ መሪዎቹን መምረጡን እንዲሁም ዶናልድ ትራምፕ ለ11 ተከሳሾች ይቅርታ ማድረጋቸውን የሚያስቃኙ ዜናዎች ተካተዋል።

  46. 55

    የሰኔ 26 ቀን 2018 የዓለም ዜና

    -በደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ዘይሴ ወረዳ የመንግሥት ታጣቂዎች በከፈቱት ጥቃት 10 ሰዎች መገደላቸዉን የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) አስታወቀ።---የቀድሞዉ የኢራን ላዕላይ መሪ አ,ያቶላሕ ዓሊ ኻምኔይ አስከሬን የሽኝት ሥርዓት ዛሬ ቴሕራን ዉስጥ ተጀመረ።ዩናይትድ ስቴትስና እስራኤል ኢራን ላይ ጦርነት በከፈቱበት ዕለት ባለፈዉ የካቲት ማብቂያ የተገደሉት ኻምኔይ ኢራንን ለ37 ዓመት መርተዋል።86 ዓመታቸዉ ነበር።--ሐሙስ ይቀበራሉ።-የጀርመን የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ዩሊያን ናግልስ ማን በከፍተኛ ግፊት ሥልጣኑን ለቀቀ።

  47. 54

    የሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

    በደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ኮሬ ዞን ተማሪዎች እስካሁን የዓመቱን የማጠቃለያ ፈተና እንዳልተፈተኑ ወላጆች ገለጹ። መምህራኑ «መንግሥት የኑሮ ውድነትን ለመደጎም ያደረገው ውዝፍ የደመወዝ ጭማሪ በተሟላ ሁኔታ አልተከፈለንም» በሚል ወደ ትምህርት ቤት አልሄዱም ተብሏል። በሰሜናዊ ናይጀሪያ ማለቂያ ባጣው ግጭት ምክንያት ታይቶ የማይታወቅ ረሀብ መከሰቱን ዛሬ የተመድ አስታወቀ። የኬንያ ፍርድ ቤት በስምንት ተማሪዎች ላይ የግድያ ክስ መሰረተ። ዛሬ ማለዳ ሩሲያ በዩክሬን ዋና ከተማ ኪየቭ ላይ ባደረሰችው ጥቃት ቢያንስ 21 ሰዎች መገደላቸውን የከተማዋ ከንቲባ አመለከቱ። 86 ሰዎችም ተጎድተዋል።

  48. 53

    የሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

    የሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም. አርእስተ ዜና አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ የሱዳኑን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል በምህጻሩ RSFን በሰብዓዊነት ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎችና በዘር ማጥፋት ወንጀል ከሰሰ ። ትውልደ-ኢትዮጵያዊቷ ሶሻል ዴሞክራት ሜላት ኪሮስ ትናንት ማክሰኞ በአሜሪካ በዴንቨር አካባቢ የተካሄደውን ምርጫ አሸነፉ። ሜላት ኪሮስ ለ15 ጊዜ የአሜሪካ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑትን ዲያና ደጌትን ነew ያሸነፉት ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን በቀጠር ዋና ከተማ ዶሀ ዛሬ ቀጥተኛ ያልሆነ ንግግር መጀመራቸው ተሰምቷል ።

  49. 52

    የሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

    የተመድ የኢቦላ ወረርሽኝ አፍሪቃን እስከ 3,6 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ያስወጣታል አለ። የኬንያ ፖሊስ በዛሬው ዕለት እገታን በመቃወም አደባባይ የወጡ ናቸው በተባሉ ሰዎች ላይ ጥይት ተኩሶ አንድ ሰው መግለደሉን እማኞች አመለከቱ። ሁለት ሰዎችም በጥይት ተጎድተዋል። የተመድ የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት በሱዳን አል ኦቢድ ጉዳይ አስቸኳይ ክርክር ሊያካሂድ መሆኑ ተገለጸ። በተጠቀሰችው ከተማ ዙሪያ የፈጥኖ ደራሹና ደጋፊዎቹ ኃይሎች መከማቸታቸው ስጋት አስከትሏል። ኢራን ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በመጪዎቹ ቀናት የመገናኘት እቅድ የለኝም አለች። ሁለት የአሜሪካ ልዑካን በኢራን ጉዳይ ለመነጋገር ዛሬ ቀጠር መግባታቸው ተዘግቧል።

  50. 51

    DW Amharic የሰኔ 22 ቀን 2018 የዓለም ዜና

    ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የሶማሊያ ፕሬዝደንት ሐሰን ሼክ ማሕሙድ ተገናኙ። ለ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና የሚቀመጡ ተማሪዎች ሞባይል ስልክ፣ ቅንጡ የእጅ ሰዓቶችና ማዳመጫዎች ወደ መፈተኛ ክፍል ይዘው መግባት ተከለከሉ። ኢትዮጵያ አንድ ቢሊዮን ዶላር የተበደረችበት ቦንድ ባለቤቶችን ከሚወክል ጊዜያዊ ኮሚቴ ጋር የዕዳ አከፋፈል ሽግሽግ ለማድረግ በመርኅ ደረጃ ከሥምምነት መደረሱን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ። የኬንያ መንግሥት ከአሜሪካ ጋር ሊፈራረም ነው የተባለው የውድ ማዕድናት ፍለጋ “ግልጽነት ይጎድለዋል” የሚል ክስ በፍርድ ቤት ቀረበበት። በጀርመን ኒደር ዛክሰን ግዛት ሽታደ ከተማ በተከፈተ ተኩስ 5 ሰዎች ተገደሉ

Type above to search every episode's transcript for a word or phrase. Matches are scoped to this podcast.

Searching…

We're indexing this podcast's transcripts for the first time — this can take a minute or two. We'll show results as soon as they're ready.

No matches for "" in this podcast's transcripts.

Showing of matches

No topics indexed yet for this podcast.

Loading reviews...

ABOUT THIS SHOW

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ ማድመጥ ትችላላችሁ። የዶይቼ ቬለ ዜና በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በየዕለቱ በቀጥታ ይደመጣል።

HOSTED BY

DW

CATEGORIES

Frequently Asked Questions

How many episodes does የዓለም ዜና have?

የዓለም ዜና currently has 50 episodes available on PodParley. New episodes are automatically indexed when they're published to the podcast feed.

What is የዓለም ዜና about?

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ ማድመጥ ትችላላችሁ። የዶይቼ ቬለ ዜና በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በየዕለቱ በቀጥታ ይደመጣል።

How often does የዓለም ዜና release new episodes?

የዓለም ዜና has 50 episodes. Check the episode list to see recent publication dates and frequency.

Where can I listen to የዓለም ዜና?

You can listen to የዓለም ዜና on PodParley by clicking any episode. We provide an embedded audio player for direct listening, and you can also subscribe via your preferred podcast app using the RSS feed.

Who hosts የዓለም ዜና?

የዓለም ዜና is created and hosted by DW.
URL copied to clipboard!