EPISODE · Jul 19, 2026 · 7 MIN
DW Amharic የሐምሌ 12 ቀን 2018 የዓለም ዜና
from የዓለም ዜና · host DW
በሶማሌ ክልል ቀብሪ በያሕ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ12 ሰዎች ሕይወት አለፈ። ለ2019 የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት 704 ቢሊዮን ብር በጀት አጸደቀ። በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ምዕራባዊ ክፍሎች፤ በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልልና በጋምቤላ ክልል በተወሰኑ አካባቢዎች በሚጥል ከባድ ዝናብ ምክንያት የጎርፍ መጥለቅለቅ ሊከሰት እንደሚችል የኢትዮጵያ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስጠነቀቀ። የታንዛኒያ ሰንደቅ የሚያውለበልብ ነዳጅ ጫኝ መርከብ ከየመን የባሕር ዳርቻ በሶማሊያ የባሕር ላይ ወንበዴዎች ታገተ። አሜሪካ ሁለት ወታደሮቿ በዮርዳኖስ ከተገደሉ በኋላ ኢራንን “ለመቅጣት” አዲስ ዙር የለሊት የአየር ላይ ድብደባ ፈጸመች።
Embed this episode
NOW PLAYING
DW Amharic የሐምሌ 12 ቀን 2018 የዓለም ዜና
No transcript for this episode yet
Similar Episodes
No similar episodes found.