EPISODE · Jan 20, 2026 · 1H
ግብርና እንደ የኃይል ምንጭ፦ የአፍሪካ የግብርና ልማት ጥያቄዎች
from The Rising South
"የኢትዮጵያ የግብርና ምርት 94 በመቶው በጥሬው ነው ወደ ውጭ የሚላከው። ምንም ዓይነት እሴት አይጨመርበትም። [...] እኔ ማየት የምፈልገው አፍሪካ ራሷን መመገብ ብቻ ሳይሆን ለቀሪው ዓለምም ምግብ ስታቀርብ ነው። አፍሪካ ምግብ ለመግዛት በየዓመቱ ከ120 ቢሊዮን ዶላር በላይ እያወጣች መቀጠል የለባትም ስለዚህ ራሷን መመገብ ብቻ ሳይሆን ከዚያም በላይ የምትተርፍ አፍሪካን፤ በቂ የምግብ ምርት ለውጭ ገበያ የምትልክ አፍሪካን ማየት እፈልጋለሁ።" ሲሉ የግብርና ሳይንቲስት እና ተመራማሪ ፀደቀ አባተ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዚህ ባለ ሁለት ክፍል የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት በክፍል አንድ ከታዋቂው የግብርና ሳይንቲስት እና ተመራማሪ ከዶ/ር ፀደቀ አባተ ጋር በመሆን አፍሪካ ለምን ልማቷን ለሌላ አካል አሳልፋ መስጠት እንደማትችል፤ እንደ እንሰት ካሉ የሀገር በቀል ሰብሎች አንስቶ እስከ መሬት ፖሊሲ እና ሌሎች ጉዳዮች እንወያያለን። በክፍል ሁለት ደግሞ ኢትዮጵያ እንደ ኦፓል ያሉ ውድ ማዕድናትን በኢትዮጵያ ምርት ገበያ ለማካተት በምታደርገው እንቅስቃሴ ላይ በማተኮር፣ በማዕድን ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት ከብስራት ከበደ (ዶ/ር) ጋር በመሆን ዳስሰነዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:
Embed this episode
NOW PLAYING
ግብርና እንደ የኃይል ምንጭ፦ የአፍሪካ የግብርና ልማት ጥያቄዎች
No transcript for this episode yet
Similar Episodes
No similar episodes found.
Similar Podcasts
No similar podcasts found.