The Rising South

PODCAST · society

The Rising South

የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

  1. 106

    ዓለም አቀፍ የነዳጅ ቀውስ እና የኢትዮጵያ የስትራቴጂካዊ አማራጮች ፍለጋ

    “ከውጭ ነዳጅ ጥገኝነት ለመውጣት የተቀናጀ ስትራቴጂ ያስፈልጋል። ትኩረታችንን የኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማትን በማዘመን፣ በፀሐይ ኃይል እና በአገር ውስጥ የተፈጥሮ ጋዝ ምርት ላይ በማድረግ የኢነርጂ ሉዓላዊነታችንን ማረጋገጥ ይኖርብናል።” ሲሉ በኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት (PSI) ወስጥ ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር ጀማል መሀመድ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡  ከነዳጅ ፖለቲካ እስከ ቀጠናዊ ደህንነት፦ ኢትዮጵያ በአዲሱ የዓለም የኃይል አሰላለፍ ውስጥ! በዛሬው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅታችን ሁለት አንገብጋቢ ጉዳዮችን ከባለሙያዎች ጋር በጥልቀት እንመረምራለን፦ የነዳጅ ጂኦ-ፖለቲካ እና የኢትዮጵያ ፈተና፦ የዓለም የነዳጅ ገበያ አለመረጋጋት በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ የሚፈጥረውን ጫና እና ሀገሪቱ የጀመረችው የጋዝ ተሽከርካሪዎች (Natural Gas Conversion) ሽግግር እንደ መፍትሄ ሊታይ ይችላል? የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት (PSI) ከፍተኛ ተመራማሪ ዶ/ር ጀማል መሀመድ ሰፊ ትንታኔ ይሰጡናል። የኢትዮጵያ እና ታንዛኒያ ወታደራዊ ትብብር፦ ሽብርተኝነትንና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን ለመከላከል በኢትዮጵያ እና በታንዛኒያ መካከል እየተገነባ ያለው ወታደራዊ ግንኙነት በቀጠናው የኃይል ሚዛን ላይ ምን ለውጥ ያመጣል? የዓለም አቀፍ ጉዳዮች ተንታኙ አብዱልናስር ምዊታ በጉዳዩ ላይ ያላቸውን እይታ ያካፍሉናል።

  2. 105

    የሥነ-ምግባር ሉዓላዊነት፦ አፍሪካ የሞራል መሠረቷን ከምዕራባውያን ተፅዕኖ እንዴት ትጠብቅ?

    "ሥነ-ምግባር ለአንድ ማህበረሰብ ህልውናው ነው። አፍሪካ የራሷን የሞራል መሠረትና እሴቶች መጠበቅ ካልቻለች፣ በግሎባላይዜሽን ማዕበል ውስጥ ማንነቷን አጥታ የሌሎች እሴቶች ተገዢ ትሆናለች።"ሲሉ የኢትዮጵያ የሥነ-ምግባር ማዕከል ፕሬዝዳንት እና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት  ዶ/ር አባ መዝገቡ ካሳ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ የዛሬው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅታችን፣ ሥነ-ምግባር ዓለም አቀፋዊ ነው ወይስ በባህልና በስልጣን የሚወሰን? የአፍሪካ ማህበረሰቦች የውጭ 'እሴቶችን' እየተቀበሉ ነው ወይስ ያለ ምርጫ እየተጫኑባቸው ነው ? ቤተሰብ፣ ትምህርት ቤቶች እና የሃይማኖት ተቋማት የሞራል መሸርሸርን ለመከላከል ምን እያደረጉ ነው? ሲል ይጠይቃል፡፡ ለዚህም የኢትዮጵያ የሥነ-ምግባር ማዕከል ፕሬዝዳንት እና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑትን ዶ/ር አባ መዝገቡ ካሳን ጋብዘናቸዋል። ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡

  3. 104

    ፓን-አፍሪካኒዝምን የማክሸፍ ዘመቻ፦ በሳህል ቀጣና ለአሸባሪዎች መረጃ የሚሰጠው ማን ነው?

    '' የተራቀቀ መረጃና ቴክኖሎጂ እየቀረበላቸው ነው፤ የፈረንሳይ ሚናም ይኸው ነው። ፈረንሳይ ለረጅም ጊዜ የጨበጠችውን ነገር በቀላሉ ለመልቀቅ ፍቃደኛ አይደለችም።[...] "እነዚህ ሶስት ሀገራት (ማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒጀር) ከሩሲያ ጋር ለመሰለፍ መወሰናቸው በዩክሬን አይን እንደ ጠላት እንዲታዩ አድርጓቸዋል። ፈረንሳይ እነዚህን ሀገራት ኢላማ ለማድረግ ከዩክሬን ጋር የደህንነት መረጃዎችን ስታስተባብር እንደነበር መረጃዎች አሉ። " ሲሉ ፓን አፍሪካኒስትና የቢዝነስና የማህበረሰብ ልማት አማካሪው ካባላ ጆን ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡በዛሬው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅታችን፣ በምዕራብ አፍሪካ እየተከሰተ ያለውን የጂኦ-ፖለቲካዊ ሽኩቻ፣ የፈረንሳይና የዩክሬን ሚስጥራዊ ጥምረት እና አዲሱ የፓን-አፍሪካኒዝም ንቅናቄ የገጠመውን ፈተና አስመልክቶ ከእንግዳችን ከፓን አፍሪካኒስት ካባላ ጆን ጋር ሰፊ ውይይት አድርገናል። መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ሙሉ ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡ 

  4. 103

    የኢትዮጵያ ቡና፣ አበባ እና ወጣቶች፦ የአፍሪካን ልማት እንደገና መመልከት

    "በአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎች ላይ ባደረግነው ጥናት መሰረት፣ በአሁኑ ወቅት ለቡና ልማት የምንጠቀምበት አካባቢ ወደ 60% የሚጠጋው በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ሊጠፋ እንደሚችል ደርሰንበታል። አንዱ የመላመጃ መንገድ ደግሞ ቡናን በከፍተኛ ከፍታ ላይ ወደሚገኙ ቦታዎች ማዛወር ሲሆን፣ እነዚህ ከፍተኛ ቦታዎች ግን የደን ሽፋናቸውን ያጡ ናቸው። ስለዚህ የ'አረንጓዴ አሻራ' እና ሌሎች የደን ልማት ተነሳሽነቶች ደኖች እንዲያገግሙ በማድረግ ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖራቸዋል።" ሲሉ የአካባቢ እና የቡና ደን ፎረም ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ታደሰ ወ/ማርያም (ዶ/ር) ስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።  በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ በቅድሚያ የአካባቢ እና የቡና ደን ፎረም ዋና ዳይሬክተር ታደሰ ወልደማርያም (ዶ/ር) ጋር በመሆን፤ የኢትዮጵያን ልዩ የቡና ቅርስ እና ያለውን ሥነ-ምህዳራዊ ጠቀሜታ እንመረምራለን፤ በማስከተልም በኢቲ ሀይላንድ ፍሎራ የእርሻ ሥራ አስኪያጅ ከሆኑት ከእመቤት ተስፋዬ ጋር በመሆን፤ በኢትዮጵያ እያደገ ያለውን የሆርቲካልቸር ዘርፍ እንቃኛለን፤ በመጨረሻም ከራሄል አዊንሱ አላቢላ (ጋና) እና ታቢታ ጆሴፍ (ኬንያ) ጋር በመሆን፤ የአፍሪካን የቅኝ ግዛት እና የዛሬው ወጣቶች ይበልጥ ሉዓላዊና የተባበረ የወደፊት ጊዜን እንዴት እየቀረጹ እንደሆነ እንወያያለን።  ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡

  5. 102

    ከሰንሰለት እስከ ስርአት፡- ያልተቋጨው የባርነት ታሪክ

    ‘‘… እጅግ በጣም በርካታ የሆኑ የተፈጥሮ ማዕድናት ያሏት አህጉር ፤ አሁንም ድረስ የቅኝ ግዛትና የባዕዳን የንግድ ሥርዓቶችን እንድትከተል መገደዷ በጣም ያሳዝናል።[…]ምክንያቱም እስከ ዛሬዋ ቀን ድረስ አፍሪካ ገና ከቅኝ ግዛት የኢኮኖሚ ጥቃትና ጭቆና እንዳልነቃች ነው የምትቀሳቀሰው። ይህ ለኔ ከዚሁ አህጉር የሚወጡ ሰዎችን ሌሎች የዓለም ክፍሎችን ለማበልጸግ በጉልበት ሠራተኝነት ከሚጠቀምበት ሥርዓት ጋር ቀጥተኛ ትስስር አለው። ይህ ሥርዓት ዛሬም ድረስ በግልጽ እየተሠራ ነው። ለምሳሌ የተፈጥሮ ማዕድኖቻችን አሁንም ከአህጉሪቱ ተነቅለው ወደ ሌላ አገር ሄደው ይመረታሉ፤ ከዚያም ተመልሰው ለእኛው ይሸጡልናል።" ሲሉ የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር እና የአፍሪካ ነፃነትና የጥቁር ሕዝቦች ንቃት -ህሊና አቀንቃኝ ዛንዲሲዌ ራዴቤ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።  በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት ዓለም በመጋቢት 25 ቀን እ.ኤ.አ የሚዘክረው ዓለም አቀፍ የባርነት እና የአትላንቲክ ባሪያ ንግድ ሰለባዎች መታሰቢያ ቀን ምክንያት አድርገን የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር እና የአፍሪካ ነፃነትና የጥቁር ሕዝቦች ንቃት -ህሊና አቀንቃኝ ዛንዲሲዌ ራዴቤ ጋር ተወያይተናል። ስለ ባርነት የሚተረከውን ታሪክ የሚቀርጸው ማን ነው? እነዚህ ታሪኮችስ በአሁኑ ወቅት በመላው ዓለም ላለው የእኩልነት ማጣት፣ ለኢኮኖሚያዊ ጥገኝነት እና ለስልጣን መዋቅሮች ያላቸው ተጽዕኖስ ምንድነው? የሚሉ ጥያቄዎችን በስፋት ዳስሰናል ። ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ ፡

  6. 101

    ሁለት የልማት ግንባሮች፣ የሳንባ ነቀርሳ በሽታን መዋጋትና ጠንካራ ኢኮኖሚን መገንባት

    "አብዛኞቹ ለቲቢ የምንጠቀማቸው መድኃኒቶች ከውጭ የሚገቡ ናቸው። ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ያስወጣናል። ለውጭ ተፅዕኖ ተጋላጭ የሆንነውም ለዚህ ነው። ስለዚህ፣ በሀገር ውስጥ የማምረት አቅምን የምናጎለብትበት ዕድል ካገኘን፣ የገንዘብ ድጋፍ ቅነሳ የሚያስከትለውን ችግር መቋቋም እንችላለን። ለአገር ውስጥ መድኃኒት አምራቾች የራሳቸውን የምርመራ መሣሪያዎችና መድኃኒቶች ማምረት እንዲችሉ አቅማቸውን ማጠናከር ይገባል።" ሲሉ የ 'ቮለንተሪ ሄልዝ ሰርቪስ' ኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር አቶ እንዳልካቸው ፍቃዱ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ በቀዳሚነት መጋቢት 15 ቀን የሚከበረውን የዓለም የሳንባ ነቀርሳ ቀንን በማሰብ በሩሲያ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የሳንባ ነቀርሳ ዋና አማካሪ ስፔሻሊስት ከሆኑት ከኢሪና ቫሲሊየቫ እንዲሁም የቪ.ኤች.ኤስ ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ከሆኑት ከአቶ እንደአልካቸው ፍቃዱ በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ የሳንባ ነቀርሳ ከድህነት፣ ከጤና ሥርዓት እና ከማኅበራዊ እውነታዎች ጋር እንዴት እንደሚገናኝ እንቃኛለን፤ በማስከተልም፣ በ10ኛው ዓለም አቀፍ የሆርቲ ፍሎራ ኤክስፖ ላይ ተገኝተን ከኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ድሪባ ኩማ እና ከአቶ ቴዎድሮስ ዘውዴ የኢትዮጵያ የአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ለኢኮኖሚው ያለውን ሚና እንዳስሳለን፡፡ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

  7. 100

    ''ያልተበደረችውን ዕዳ የምትከፍለው አፍሪካ'':-የአየር ንብረት ለውጥ እና 'ዘመናዊ' ተብለው የቀረቡ የግብርና ወጥመዶች

    "ዓለም ቀደም ሲል ከነበረው የአስተሳሰብ ዘይቤ በተለየ መንገድ ማሰብ ይኖርበታል። መሰረታዊ ነገሮች መለወጥ አለባቸው፤ ምክንያቱም አሁን ያለው ሁኔታ ፍትሃዊ ያልሆነና ዘላቂነት የሌለው ነው። ስለዚህ፣ የምዕራባውያን ዓለም ለአየር ንብረት ለውጥ ካደረጉት አስተዋጽኦ ጋር የሚመጣጠን በቂ ድጋፍ የማቅረብ ኃላፊነትን ሊወስዱ ይገባል፡፡" ሲሉ የግብርና ሳይንቲስት እና ተመራማሪ ፀደቀ አባተ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ በክፍል አንድ የአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካን ግብርና እንዴት እየቀየረው እንደሆነና አፍሪካ ለዓለም አቀፉ የጋዝ ልቀት የምታበረክተው አስተዋጽዎ በጣም አነስተኛ ቢሆንም፣ ለምን የከፋውን ጫና ለመሸከም እንደተገደደች የግብርና ሳይንቲስት እና ተመራማሪ ከሆኑት ፀደቀ አባተ (ዶ/ር) ጋር ባደረግነው ቆይታ የዳሰስነው ሲሆን፤ በሁለተኛው ክፍል ደግሞ፣ የማህበረሰብ ጤና ባለሙያ ከሆኑት ከዶ/ር ሩት ዳኛቸው ጋር በመሆን፣ በኢትዮጵያውያን ወጣቶች ዘንድ እየተስፋፋ የመጣውን የሱስ ተገዥነት እና የአእምሮ ጤና ቀውስ እንፈትሻለን፤ ለዚህም ዝምተኛ የህዝብ ጤና ተግዳሮት መንስኤ የሆኑትን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ስርዓታዊ ጫናዎችን በዝርዝር እንመለከታለን።ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ 

  8. 99

    የአእምሯዊ ንብረት መብት ተጽዕኖ በአፍሪካ ፋርማሲዩቲካልስ ኢንዱስትሪ ላይ

    “አብዛኞቹ የተከናወኑት በምዕራባውያን እና በአውሮፓውያን ነው። ስኮቶች፣ እስያውያን እና አፍሪካውያን ደግሞ በማህበረሰብ ፋይናንስ እና መሰረተ ልማቶች ባላቸው ሰፊ ተደራሽነት ምክንያት ኢንቨስት እያደረጉ ነው። ስለዚህ፣ በርካታ ኢንቨስትመንቶች እንዳሉ እስማማለሁ:: እናም ኢንቨስትመንቱ ሊመለስላቸው ይገባል። ነገር ግን፣ ይህ መሆን ያለበት የፈጠራ ስራዎችን እና ምርምርን በማገድ መሆን የለበትም።” ሲሉ የኪሊች ኤስትሮ ባዮቴክ ኃ.የተ.የግ.ማ መስራችና ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ እንዲሁም የኢትዮጵያ ፋርማሲስቶች ማህበር ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶ/ር ዳንኤል ዋቅቶሌ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዛሬው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት በቀዳሚነት የኢትዮጵያ ፋርማሲስቶች ማህበር ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዳንኤል ዋቅቶሌ ጋር ስለ አእምሯዊ ንብረት መብት እና መድኃኒት አቅርቦት እንወያያለን። በሁለተኛው ክፍል ከመጋቢት 7–9 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ የተካሄደው የደቡብ አፍሪካ-ኢትዮጵያ የንግድ ፎረም ላይ ተገኝተን የደቡብ አፍሪካ የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ውድድር ሚኒስቴር የኤክስፖርትና ማርኬቲንግ ዋና ዳይሬክተር ዛኔሌ ሳኒን እንዲሁም የሉንየዚ ፋርምስ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሳምኬሊሲዌ ሲቶሌን በንግድና ኢንቨስትመንት ዙሪያ አነጋግረናቸዋል።ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ 

  9. 98

    መረጃ፣ ቋንቋ እና ሉዓላዊነት፦ የአፍሪካ የትርክት ትግል

    “ከዚህ ቀደም ምዕራባውያን በአካል መጥተው የወረሩን ጊዜያት ነበሩ። የአፍሪካን ሕዝብ በቅኝ ገዝተዋል። ዛሬ ግን ሥርዓቱ ሙሉ በሙሉ ተቀይሯል። አሁን ደግሞ በመረጃ ቋቶቻቸው አማካኝነት ሊገዙን እየሞከሩ ነው። የማይወክሉንን ነገሮች ሁሉ እየሰበሰቡ ‘የእናንተ ተሞክሮ ይህ ነው’ ይሉናል። ነገር ግን ያ እኛን አይገልጸንም። ለዚህ ነው አፍሪካውያን የራሳችን የሆነ ‘የመረጃ ስብስብ’ እና የራሳችን የሆነ የቋንቋ ማቀነባበሪያ ዘዴ (Language processing) ሊኖረን የሚገባው።” ሲሉ በርቀት እና ኢ-ለርኒንግ ትምህርት ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑት ዶ/ር አደራጀው ምህረት ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ስለ አፍሪካ ምን ማወቅ እንዳለበት የሚወስነው ማነው? አፍሪካስ የራሷን ታሪክ በየትኛው ቋንቋ ትናገራለች? በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ ከዶ/ር አደራጀው ምህረት ጋር ስለ "አልጎሪዝም የበላይነት" እንወያያለን። እንዲሁም በኢትዮጵያ የኩባ ከአምባሳደር ሜይሊን ሱዋሬዝ አልቫሬዝ እና ሌሎችም ጋር በመሆን ዓለም አቀፍ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ቀንን እናከብራለን፤ በኮድ እና በባህል ውስጥ ያለውን "የትርክት ሉዓላዊነት" ትግልም በጥልቀት እንመረምራለን። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡

  10. 97

    ከአፍ መፍቻ ቋንቋ እስከ ፋይናንስ አቅም፦ የአፍሪካ መዋቅራዊ ሽግግር

    “የአፍሪካ የዕውቀት ሥርዓቶች አብዛኛውን ጊዜ የሥነ-ምግባር ወጎችን እና የማኅበረሰብ ትውስታዎችን ያካተቱ ነበሩ። እነዚህ ደግሞ በአፍሪካ ወይም በቅኝ ተገዢ አገሮች ላይ በተጫነው በጽሑፍ በሰፈረ ቀጥተኛ ቀኖናዊ (dogmatic) እና ቢሮክራሲያዊ አመክንዮ ሙሉ በሙሉ ተተኩ። […]ስለዚህ፣ ቋንቋ የአስተዳደራዊ ምክንያታዊነት መሣሪያ በመሆን፣ ተለዋዋጭ የነበሩ ማኅበራዊ ሥርዓቶችን ወደ ደረቅ፣ ሕጋዊ እና ቀኖናዊ የፖለቲካ መዋቅሮች ለውጦታል።” ሲሉ በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊ ሳይንስ እና ሂውማኒቲስ ኮሌጅ ዲን የሆኑት ዶ/ር አስቻለው ታደሰ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅታችን፣ በመጀመሪያው ክፍል በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊ ሳይንስ እና ሂውማኒቲስ ኮሌጅ ዲን ከሆኑት ከዶ/ር አስቻለው ታደሰ ጋር በመሆን ዓለም አቀፍ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ቀንን ስናከብር የቅኝ ግዛት ቋንቋዎች በአፍሪካ የእውቀት ስርዓት እና በማንነት ላይ ያሳረፉትን ዘላቂ ተጽዕኖ እንዳስሳለን። በተጨማሪም ከአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም 2026 የተገኙ ጠቃሚ ግንዛቤዎችን— ከክላቨር ጋቴቴ፣ ከዶ/ር ጁማ ሙክዋና፣ ከቤንጃሚን ኤቪታ ኦማ እና ከፋቱ ኪንቴህ ጋር በመሆን—ስለ ፋይናንስ ሉዓላዊነት፣ ስለ አፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና ፣ ስለ ወጣቶች ፈጠራ እና አህጉሪቱ ለኢኮኖሚ ነፃነት ስለምታደርገው ጥረት በክፍል ሁለት ዝግጅታችን ዳስሰነዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡

  11. 96

    የመካከለኛው ምሥራቅ ውጥረት እና የአፍሪካ አህጉራዊ የልማት አማራጮች

    "በቅርቡ በኢራን የታዩትን ክስተቶች፣ አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ በከፈቱት ጥቃት፣ እንዲሁም ትንሽ ቀደም ብሎ በቬንዙዌላ የሆነውን ስንመለከት፤ እነዚህ ክስተቶች ዓለም አቀፋዊውን መዋቅር እየቀየረ ያለ አዲስ ሥርዓት መኖሩን ይነግሩናል። አሁን ባለንበት ሁኔታም የኃይል ፖለቲካ ከሕግ የበላይነት በላይ እየገነነ መጥቷል። በዚህ ሂደት ውስጥ ደግሞ ይበልጥ ተጋላጭ የሆኑት የደቡባዊ ዓለም ሀገራት ያላደጉና በማደግ ላይ ያሉ አገራት ናቸው።" ሲሉ የልማት ኢኮኖሚስቱ  እንዳልካቸው ስሜ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅታችን፣ በመጀመሪያው ክፍል ከልማት ኢኮኖሚስቱ እንዳልካቸው ስሜ (ዶ/ር) ጋር በመሆን ዓለም አቀፋዊ የጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች—በተለይም በኢራን ዙሪያ ያለው አለመረጋጋት—በአፍሪካ የኢነርጂ ገበያ፣ የንግድ መስመሮች እና የኢኮኖሚ ስትራቴጂ ላይ ምን ተፅዕኖ ያሳድራሉ? የሚሉትን ጥያቄዎች የምንዳስስ ሲሆን፤ በክፍል ሁለት፦ የ2025 የዓለም አቀፍ የረሃብ መረጃ ጠቋሚ ግኝቶችን የአፍሪካ ህብረት ግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ሰማያዊ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ጥበቃ ኮሚሽነር ከሆኑት ከሙሴ ቪላካቲ እና በኢትዮጵያ የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ተመራማሪ ከሆኑት ደሳለኝ ቤኛ (ዶ/ር) ጋር ዳስሰነዋል። ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ 

  12. 95

    "ሩሲያ የዲሞክራሲያችን ጋሻ ናት" — ፕሬዝዳንት ፋውስቲን አርካንጅ ቱዋዴራ

    የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ፋውስቲን አርካንጅ ቱዋዴራ ከየካቲት 26 እስከ የካቲት 27 ፣ 2018 ዓ.ም በሩሲያ ሞስኮ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ከሩሲያ አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል። "የሉዓላዊነት መርሆዎችን እና የሰላም ጥረቶችን እንደግፋለን። የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ሕዝቧ አስቸጋሪ ጊዜያትን ያሳለፉ በመሆኑ፣ በዓለም ላይ ሰላም እንዲሰፍን ትፈልጋለች። ለዚያ ግብ ደግሞ መሥራት ይኖርብናል። ወደ ውይይት እና ድርድር ጠረጴዛ መቅረብ እና ከፍተኛ የሰው ሕይወት መጥፋትና የመሠረተ ልማት ውድመት እያስከተሉ ያሉ ጥቃቶችን በቀጥታ መፍታት አስፈላጊ መሆኑን እናምናለን።" ሲሉ የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ፋውስቲን አርካንጅ ቱዋዴራ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዛሬው የራይዚንግ ሳዉዝ ዝግጅታችን የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ፋውስቲን-አርቻንጅ ቱዋዴራ ስለ ቀጠናው ሰላም እና ስለ ሩሲያ ድጋፍ ከስፑትኒክ አፍሪካ ጋር ያደረጉት ልዩ ቆይታ፣ በእስራኤል፣ አሜሪካ እና ኢራን መካከል ስላለው ፍጥጫ የዓለም አቀፍ ጉዳዮች ተንታኙ ሞሃመድ ሲራጅ የሚሰጡት ሰፊ ማብራሪያ። የሀገርን ሉዓላዊነት ያስከበረው ታሪካዊው የካራማራ ድል ለኢትዮጵያ አንድነት ያለውን ፋይዳ የቆሮማሽ ማህበር ሰብሳቢ አቶ ደቻሳ አንገቻ ጋር ያደረግነው ውይይት ተካትተዋል። ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

  13. 94

    ሉዓላዊነት ላይ ያነጣጠረ ጥቃት፦ በታለመ ግድያ የታወከው የመካከለኛው ምስራቅ ሰላም

    “ ከ1945 ጀምሮ ለዓለም መረጋጋት መሠረት የነበሩት ዘርፈ-ብዙ ሥርዓቶችና ስምምነቶች እየፈራረሱ ባሉበት ዓለም ውስጥ እንገኛለን። እስራኤልና አሜሪካ በኢራን ላይ የፈጸሙት ድርጊት በምንም መመዘኛ በሕግ የተደገፈ አይደለም፤ ይልቁንም የተባበሩት መንግሥታትን ቻርተር የጣሰ፣[...] ዲፕሎማሲን ለወታደራዊ ጥቃት እንደ መሸፈኛ መጠቀም፣ ለወደፊት ዓለም አቀፍ መረጋጋት አስፈላጊ የሆነውን እምነት ለዘለቄታው ያጠፋዋል።” ሲሉ በአፍሪካ ቀንድ እና በመካከለኛው ምስራቅ ጉዳዮች ተመራማሪ እና ተንታኝ የሆኑት ራሺድ አብዲ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ ስለመጣው ውጥረት በአፍሪካ ቀንድ እና በመካከለኛው ምስራቅ ጉዳዮች ተመራማሪ እና ተንታኝ ራሺድ አብዲ ጋር በመሆን ስለ ዓለም አቀፍ ሕግ የወደፊት ዕጣ ፈንታ በመጀመሪያው ክፍል በሰፊው እንዳስሳለን። በሁለተኛው ክፍል ደግሞ የሚዲያ ባለሙያ እና የድምፅ ተዋናይ ኮስሞ ሚለር ጋር ስለ ቋንቋ፣ ስለ ቅኝ ግዛት እና ስለ አፍሪካ ልማት ጥልቅ እንዲሁም የጂኦፖለቲካ ጉዳዮችን ከባህላዊ ሉዓላዊነት ጋር አጣምረን እንዳስሳለን።ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

  14. 93

    ከባዕድ ትርክት ወደ አፍሪካዊ እውነት፦ የስፑትኒክ አፍሪካ የኢትዮጵያ ቢሮ የአንድ ዓመት ጉዞ

    “አፍሪካውያን የራሳቸውን ታሪክ በራሳቸው መንገድ እና አተራረክ ዘዬ ማቅረብ አለባቸው የሚል ትልቅ የፓን-አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ አለ። […] ያ ትግል ረጅም ዓመት ሄዷል፣ ግን ያን ያህል ውጤታማ መሆን አልቻለም። ውጤታማ እንዳይሆን ያደረገው ትልቁ ምክንያት የመረጃ ክፍተት ነው። መረጃ ደግሞ ኃይል መሆኑን የምታውቀው ቢያንስ የራስህ ባይሆን እንኳን አንተ የምትቆጣጠረው ሚዲያ ወይም በአንተ መጫወቻ ሜዳ ላይ መሰረት ያደረገ ሲሆን ነው።” ሲል በስፑትኒክ አፍሪካ የኢትዮጵያ ቢሮ አዘጋጅ እና አቅራቢ የሆነው ዐብይ ሀብታሙ ተናግሯል። በዚህኛው ልዩ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ ስፑትኒክ አፍሪካ በኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ከፍቶ ስርጭት የጀመረበትን 1ኛ ዓመት አስመልክቶ የመጀመሪያው ዓመት የሥራ መልኮቻችን ላይ ቅኝት አድርገናል። ለዚህም በኢትዮጵያ የስፑትኒክ አፍሪካ አዘጋጅ እና አቅራቢ ከዐብይ ሀብታሙ እና ዘላለም ደምሴ ጋር ቆይታ አድርገናል። “እንደ ስፑትኒክ ያሉ ትልቅ አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን፣ ተሰሚነት ያላቸው መገናኛ ብዙሃን በቋንቋችንም፣ በእንግሊዝኛውም ደግሞ ስራ መጀመራቸው አፍሪካውያን ስለ አፍሪካ፣ ስለ ራሳችን ያለንን ግምት ከመቀየር አንጻር በጣም ትልቅ አስተዋጽኦ አለው።” ሲል በስፑትኒክ አፍሪካ የኢትዮጵያ ቢሮአዘጋጅ እና አቅራቢ የሆነው ዘላለም ደምሴ አክሏል። ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

  15. 92

    የአፍሪካ ድምፅ በአፍሪካዊያን፦ ስፑትኒክ አፍሪካ በኢትዮጵያ !

    “ስፑትኒክን በተመለከተ ፣ እኛ አማራጭን ብቻ ነው የምናቀርበው። የተለየ የዕይታ ነጥብ እያቀረብን ነው፤ እንዲሁም ለደቡባዊው ዓለም አገራት ድምፅ ለመስጠት እየሞከርን ነው። ስለዚህ፣ እኛ ምንም ዓይነት ነገር በማንም ላይ እየጫንን አይደለም። እኛ ያልተነገሩትን ነገሮች እየተናገርን ነው፤ አድማጮቻችን እና አንባቢዎቻችን ደግሞ የራሳቸውን መደምደሚያ እንዲያሳርፉ እንጋብዛለን። ስለዚህ፣ ለደቡባዊው ዓለም አገራት በመገናኛ ብዙኃን ዓለም ውስጥ እንዲህ ዓይነት አማራጭ ማግኘታቸው ትልቅ ዕድል ነው።" ሲሉ የስፑትኒክ አፍሪካ የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ቢሮ ኃላፊ አሌክሳንደር ሺፒን ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዚህኛው ልዩ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ ስፑትኒክ አፍሪካ በኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ከፍቶ ስርጭት የጀመረበትን 1ኛ ዓመት አስመልክቶ የመጀምሪያው ዓመት የሥራ ሂድት እና አጠቃላይ መልኮችን አስመልክቶ የስፑትኒክ አፍሪካ የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ቢሮ ኃላፊ አሌክሳንደር ሺፒን፣ ማኔጂንግ ኤዲተር ፀጋዬ ወንደሰን እንዲሁም አዘጋጅ እና አቅራቢ ከሆነችው ኤደን ተሾመ ጋር ቆይታ አድርገናል። ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

  16. 91

    የዓድዋ ድል፦ የኢትዮጵያዊያንን የትብብር አቅም የገለጠ የአፍሪካዊያን ኩራት

    ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ክብርና ችሎታ ምልክት ሆኗል።[...]ፓን አፍሪካኒስቶች ማንሰራራት የቻሉት የ1896 እ.ኤ.አ የአድዋ ድልን ተከትሎ ነው። ስለዚህ እነዚህ ሰዎች ኢትዮጵያን እንደ ማረጋገጫ ወስደው፣ አፍሪካውያን የአውሮፓን የበላይነትና ቅኝ ግዛት መቋቋም እንደሚችሉ ተመልክተዋል። ሲሉ በወሎ ዩኒቨርስቲ የታሪክ ትምህርት ረዳት ፕሮፌሰር አሰፋ ባልቻ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዛሬው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅታችን በኢትዮጵያ ለ130ኛ ጊዜ እየተከበረ ያለውን የዓድዋ ድል በዓል መነሻ አድርገን ሉዓላዊነትን በሶስት መልኩ ቃኝተነዋል። በቀዳሚነት ኢትዮጵያ በዓድዋ የተቀዳጀችውን ድል መነሻ አድርገን ለአፍሪካ ስላለው ትርጓሜ በወሎ ዩኒቨርስቲ የታሪክ ትምህርት ረዳት ፕሮፌሰር አሰፋ ባልቻ ጋር በሰፊው ዳስሰናል። በሁለተኝዉ ክፍል የእጅ አዙር ቅኝ ግዛት መገለጫ ስለሆነዉ ቋንቋና ሉዓላዊነትም የሚዲያ ባለሙያ እና የድምፅ ተዋናይ ኮስሞ ሚለር ጋር በሁለተኛው ክፍል ቆይታ አድርገናል። በመጨረሻም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ላይ ትኩረታችንን አድርገን ከ'ኤአይ' የሚሰጠንን መረጃ ማን ይወስናል ስንል ስንል ለ21ኛው መቶ ክፍለዘመን የአፍሪካ የትርክት መልክ አማራጭ ሀሳቦችን ከዲጂታል አስተዳደርና ትራንስፎርሜሽን ባለሙያው እስክንድር ቸርነት ጋር ፈትሸናልን። ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

  17. 90

    የቤተሰብ ዕቅድ እና የስነ-ተዋልዶ ጤና አገልግሎትን ከእርዳታ ጥገኝነት ነጻ የማድረግ ጅምር በኢትዮጵያ

    “የጤናውን ሴክተር ስንመለከት ጤና ብቻውን በአንድ የሚቆም።[…] የዓለም ጤና ድርጅት ደግሞ 'Health in All Policies' ነው የሚለው። የጤና ፖሊሲዎች በሁሉም ፖሊሲዎች ውስጥ መኖር አለባቸው። ምክንያቱም ግብርና ብንለው፣ ትምህርት ብንል፣ ሁሉም ብንላቸው የጤና ፖሊሲ ከሌላቸው ሙሉ አይሆኑም፤ ምክንያቱም ዋናው ጤና ስለሆነ ማለት ነው።” ሲሉ በጤና ሚኒስቴር የስነ-ተዋልዶ ጤና፣ የቤተሰብ እቅድ፣ የአፍላ ወጣቶች እና ወጣቶች ፕሮግራም ኃላፊ ዶ/ር አለማየሁ ሁንዱማ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት በመጀመሪያው ክፍል በጤና ሚኒስቴር የስነ-ተዋልዶ ጤና፣ የቤተሰብ እቅድ፣ የአፍላ ወጣቶች እና ወጣቶች ፕሮግራም ኃላፊ ከሆኑት ዶ/ር አለማየሁ ሁንዱማ ጋር በመሆን መንግስት ከመደበኛ ብሄራዊ በጀቱ ወደ 14 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ለፕሮግራሙ በመመደብ ከእርዳታ ጥገኝነት ነጻ የሆነ የጤና ስርዓትን እውን የማድረግ ሂደት እንመለከታለን። በሁለተኛው ክፍል ደግሞ የኢትዮጵያ ፈጣን የከተሞች እድገት እና እየጨመረ ስለመጣው የቤት ፍላጎት ጉዳይ በሪል ሰቴት ዘርፍ ላይ ከፍተኛ የማርኬቲንግ ባለሙያ እና አማካሪ ከሆኑት ኢንጂነር ቸርነት መንግስቴ ጋር ያደረግነውን ውይይት አካትተናል። ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

  18. 89

    ዓለምአቀፍ የሬዲዮ ቀን፦ ከሬዲዮ ሞስኮ እስከ ስፑትኒክ የሩሲያ የመረጃ ተደራሽነት በአፍሪካ

    ዛሬ አለምዓቀፉ የሬዲዮ ቀን በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። ስፑትኒክ አፍሪካም በአዲስ አበባ ማህበረሰብ ሬዲዮ 99.4 ኢትዮጵያን ፣ አፍሪካን እና መላው ዓለምን የሚዳስሱ ዝግጅቶችን በአማርኛና በእንግሊዝኛ እያቀረበ ይገኛል። ‘’ [...]ስፑትኒክ አፍሪካ በኢትዮጵያ በከፈተው ቢሮ ኢትዮጵያን እና አፍሪካን የሚመጥኑ ጠንካራ ይዘቶችን እየሰራ ነው።[...] የስፑትኒክ ጋዜጠኞችን በደቡብ አሜሪካ ሀገራት ጥናት ምርምርን ሲያቀርቡ አግኝቻቸው ነበር። ይህ የሩስያን ቀናነትና አብሮ የመስራት ፍላጎት የሚያሳይ ነው።” ሲሉ አንጋፋው ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዛሬ የራይዚንግ ሳዉዝ ዝግጅታችን ዓለም አቀፍ የሬዲዮ ቀንን መነሻ በማድረግ ፣ ከሬዲዮ ሞስኮ አእስከ ስፑትኒክ በሚል ርዐእስ አእለቱን አእዘክራለን። ሬዲዮ ከሌሎች የመገናኛ አዉታሮች የተለዩ የሚያደርጉትን ባህሪያትና ስፑትኒክ አፍሪካ በአዲስ አበባ የቅርንጫፍ ቢሮውን መክፈቱ በመረጃ ፍሰት ላይ የሚኖረውን ሚናም እንዳስሳለን።ለዚህም አንጋፋዎቹን ጋዜጠኞች እና የሚዲያ ባለሙያዎች ተፈሪ ዓለሙ እና ጥበቡ በለጠ ጋር በተጨማሪም ስለ ሬዲዮ ሞስኮ ትዝታቸውን ካካፈሉን ከአቶ ማሞ መንገሻ ጋር ቆይታ አድርገናል፡፡ ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

  19. 88

    የኢትዮጵያ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዩኒቨርሲቲ የመገንባት እቅድ

    “ለዓመታት በአፍሪካ ውስጥ ስንጠቀምባቸው የቆዩትን መረጃዎች (Data) የሀገር በቀል ማድረግ ይገባናል። ምክንያቱም የ-AI ሞዴሎች የሚቀረጹት በሰለጠኑበት መረጃ ልክ ነው። ያ መረጃ በብዛት የመነጨው ከሰሜናዊው የዓለም ክፍል ስለሆነ፣ የሚያንጸባርቀው የእነሱን ማንነት እንጂ የእኛን አይደለም። ስለዚህ በራሳችን መረጃዎች የተደራጀ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ሊኖረን ይገባል።” ሲሉ ከፍተኛ የትምህርት ባለሙያ የሆኑት ረዳት ፕ/ር አደራጀው ምህረት ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል፣ ከፍተኛ የትምህርት ባለሙያ ከሆኑት ከረዳት ፕ/ር አደራጀው ምህረት ጋር በመሆን ኢትዮጵያ ልዩ የሆነ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም ያላትን እቅድ የምንመለከት ሲሆን፤ በሁለተኛው ክፍልም የ2026ቱ የTenDX አዲስ አበባ ጉባኤ ላይ ተገኝተን ስለ ዲጂታል የክፍያ ስርዓቶች፣ ዲጂታል መታወቂያ እና ፓን-አፍሪካዊ የፋይናንስ መሠረተ ልማቶች በካምፓስ ፕላስ ቴክኖሎጂስ የመካከለኛው ምስራቅ እና አፍሪካ ም/ል ፕሬዝዳንት እና ም/ል ማኔጂንግ ዳ/ር የሆኑትን አዲል አህመድን እና በኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ የባለድርሻ አካላት ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር የሆኑትን ሳሚናስ ሰይፉን አነጋግረናቸዋል። ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

  20. 87

    የባህል ኃይል፦ ባሕላዊ አመራር፣ ፋሽን እና የአፍሪካ የወደፊት ጉዞ

    “የዓለም አቀፍ ሕግ፣ በምዕራባውያን ወገን ሕጎች የሚጥሱትን እንዲታሰሩ የሚያደርግ ነው። አንድ አፍሪካዊ መሪ በፖለቲካዊ መልኩ የአፍሪካን መንገድ ለመከተል ከወሰነ፣ ኢላማ ይደረጋል። በአንተ ላይ መጥፎ የሆኑ ስሞችን በመለጠፍ መገናኛ ብዙኃንን ተጠቅመው ሕዝቡ አንተን በመጥፎ ዓይን እንዲመለከትህ ማድረግ ይጀምራሉ። ይህንንም በአንተ ላይ የሚወስዱትን እርምጃ ትክክለኛ እንደሆነ ለማስመስል ይጠቀሙበታል። እስካሁንም ያለው አካሄድ ያው ነው።” ሲሉ በጋና ባሕላዊ መሪ እና የ‘ዘ ቴስት ኦፍ አፍሪካ’ ተባባሪ መስራች የሆኑት ቴንጎል ኬፕሌማኒ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል፣ በጋና ባሕላዊ መሪ እና የ‘ዘ ቴስት ኦፍ አፍሪካ’ ተባባሪ መስራች እና የ‘ካልቸራል ዋንነስ ፌስቲቫል’ አዘጋጅ ቴንጎል ኬፕሌማኒ ጋር በመሆን — በፍጥነት እየተለወጠ ባለው ዓለም ውስጥ የአፍሪካ ወጎች እንዴት አግባብነታቸውን ጠብቀው ሊቀጥሉ እንደሚችሉ እንወያያለን። በሁለተኛው ክፍል ደግሞ የ‘አፍሪካ ሞዛይክ’ የፋሽን መድረክን አስታከን ከቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አረጋ እና ከታዋቂው ሙዚቀኛና አርቲስት ስለሺ ደምሴ (ጋሼ አበራ ሞላ) ጋር ስለ ባህል ዲፕሎማሲ እና ተያያዥ ጉዳዮች ያደረግነውን ቆይታ አካትተናል። ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

  21. 86

    የኢትዮጵያ የባህር በር ፍላጎት እና የደቡባዊው ዓለም የቴክኖሎጂ ሽግግር

    "[ኢትዮጵያ] በአፍሪካ በሕዝብ ቁጥር ብዛት ሁለተኛዋ ሀገር እንደመሆኗ፣ በአንድ [በጅቡቲ] ወደብ ላይ ጥገኛ መሆን በጣም አስቸጋሪ ነው። ስለዚህ አሁን ፍላጎታችንና ጥቅማችን በጣም የተለያየ ነው። በዚህም ምክንያት ተጨማሪ ወደቦችን መጠቀም፣ መመልከት ወይም መፈለግ እጅግ አስፈላጊ ነው።" ሲሉ በጅማ ዩኒቨርሲቲ የምስራቅ አፍሪካ የዲፕሎማሲ እና የፖለቲካ ታሪክ መምህር የሆኑት አቶ በላይ በየነ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዛሬው የራይዚንግ ሳውዝ የሁለት ክፍል ዝግጅታችን፣ በመጀመሪያው ክፍል፣ የኢትዮጵያ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በርበራን ከጎበኘ በኋላ፣ የኢትዮጵያን እየተለወጠ የመጣውን የባህር ላይ እና የጂኦ-ፖለቲካ ስትራቴጂ እንመረምራለን። ለዚህም በጅማ ዩኒቨርሲቲ የምስራቅ አፍሪካ የዲፕሎማሲ እና የፖለቲካ ታሪክ መምህር ከሆኑት ከአቶ በላይ በየነ ጋር በዝርዝር እንቃኛለን። በሁለተኛው ክፍል ደግሞ፣ በደቡባዊው ዓለም ወስጥ በመካሄድ ላይ ስላለው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ (ኢ- ሞቢሊቲ) አብዮት እንዳስሳለን። ለዚህም በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የመካኒካል፣ ኬሚካል እና ማቴሪያል ሳይንስ ምህንድስና ኮሌጅ ዲን ከሆኑት ከዶ/ር ሽመልስ ለማ ጋር ቆይታ አድርገናል።  ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

  22. 85

    ከቅኝ ግዛት እስከ ስልታዊ አጋርነት፡- በዲፕሎማሲው መስክ የቀጠሉ ሁነቶች

    የደቡባዊው ዓለም ሀገራት ከምንጊዜውም በላይ የእርስ በእርስ ግንኙነታቸውን ማጠናከር የግድ የሚላቸው ጊዜ ላይ ደርሰዋል፡፡ የምዕራቡ ዓለም ሀገራት የማእድን ሀብታቸውን ሲሉ በታዳጊ ሀገራት ላይ ቀጥተኛና ህገወጥ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት መፈጸም ቀጥለዋል፡፡  “ይህ የተመድ ድክመት ነው። ምክንያቱም እነዚህ አገራት በሙሉ፣ ድሃም ይሁኑ ሀብታም፣ ነፃ አገራት ናቸው። አሜሪካ በእነዚህ አገራት ላይ ጥቃት መፈጸም የለባትም። ይህ የኢምፔሪያሊዝም መገለጫ ነው። በመሆኑም ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በአንድነት ሊቆም እና በነፃና ሉዓላዊ አገራት ላይ የሚፈጸመውን የጥቃት ድርጊት መቃወም አለበት።” ሲሉ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ኢኮኖሚያዊ ግኑኝነት ባለሙያ የሆኑት ዶ/ር ዱጋሳ ሙሉጌታ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዚህ ባለ ሁለት ክፍል የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል፣ ከዶ/ር ዱጋሳ ሙሉጌታ ጋር በመሆን የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ የ2026 ዓመታዊ ጋዜጣዊ ማብራሪያቸውን መነሻ አድርገን ሞስኮን ወደ ደቡባዊ ዓለም /Global South/ እያደረገች ያለውን ከፍተኛ ትኩረት እንወያያለን። የቢትኮይን ባለሙያ ከሆነው ቃል ካሳ ጋር የቢትኮይን (Bitcoin) ኢንቨስትመንትን መሰረት በማድረግ የኢትዮጵያን ዲጂታልፋይናንስ ትኩረት መነሻ አድርገን ፣ አማራጩ እውነተኛ የፋይናንስ ሉዓላዊነትን ሊያመጣ ይችላልን? የውጭ ምንዛሪ እጥረትንስ ይቀርፋል? በሚሉት ነጥቦች ዙሪያ ያደረግነውን ውይይት በሁለተኛው የዝግጅት ክፍላች ዳስሰነዋል፡፡ ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

  23. 84

    የሉዓላዊነት ጉዞ፦ ኢትዮጵያ በጤና፣ በምግብ እና በአየር ትራንስፖርት ዘርፎች እያመጣች ያለችው አዲስ ለውጥ

    "የኢትዮጵያ የምግብ እና የመድኃኒት ባለሥልጣን የደረጃ ሶስት (Maturity Level 3) እውቅናን ማግኘቱ ለሀገሪቱ ብቻ ሳይሆን ለቀጠናው፣ እንዲሁም ለእኛ እንደ ኢንዱስትሪ ባለቤቶች ጨዋታ ቀያሪ ትልቅ ክስተት ነው።[...]የምስክር ወረቀቱን በቀላሉ በመጠቀም በኢትዮጵያ የተመረተን ማንኛውንም ምርት በመላው አፍሪካ አልፎም ከዚያ በላይ ማሰራጨት እንችላለን።" ሲሉ 'ፋርማኮሎጂስት' እና የኢትዮጵያ የፋርማሲ ባለሙያዎች ማህበር ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዳንኤል ዋክቶሌ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት በቀዳሚነት ፋርማኮሎጂስት እና የኢትዮጵያ የፋርማሲ ባለሙያዎች ማህበር ፕሬዝዳንት ከሆኑት ከዶ/ር ዳንኤል ዋክቶሌ ጋር በኢትዮጵያ የመድኃኒት ዘርፍ መንግስት የገበያውን መጠን እስከ 2030 ድረስ ወደ $3.6 ቢሊዮን ለማሳደግ የሰነቀውን ዕቅድ እንቃኛለን። በመቀጠል የኢትዮጵያን የስንዴ ምርት እድገት ከከፍተኛ የግብርና ተመራማሪዉ ጸደቀ አባተ (ዶ/ር) ጋር እናነሳለን።በመጨረሻም በኢትዮጵያ ሲቪል አቪየሽን ባለሥልጣን ከፍተኛ የአቪየሽን ባለሙያ ከሆኑት ከአቶ እንዳለ ተሾመ ጋር ሆነን ቦይንግ ስለ አፍሪካ አቪየሽን ዕድገት ያስቀመጠውን ትንበያ እና የኢትዮጵያ ልዩ ሚና እንመረምራለን።  ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

  24. 83

    ኃይል ወይስ ሕግ፦ ተመድ አሁንም በሕግ የሚመራ ተቋም ነውን?

    “የቪቶ (ድምፅን በድምጽ የመሻር) ስልጣን ያለአግባብ ጥቅም ላይ ውሏል፤ ተበድሏልም። በ2003 በኢራቅ ላይ በአሜሪካ ጥቃት ሲሰነዘር ሩሲያ ለዚያ ወረራ እና ወታደራዊ ጣልቃገብነት ድምፅ አልሰጠችም። […] አፍሪካ በ2026 ያላትን ቋሚ ያልሆኑ መቀመጫዎች ብንመለከት እንኳ፣ የቪቶ ስልጣን ባላቸው አምስቱ ቋሚ አባላት እና የቪቶ ስልጣን በሌላቸው ቋሚ ባልሆኑ አባላት መካከል ያለው ልዩነት ምንም አይነት ትርጉም አይሰጥም። ይህ ሁኔታ በእውነቱ ዓለም አቀፍ ህግን መሳቂያ ያደርገዋል።” ሲሉ በደቡብ አፍሪካ ዩኒሳ የታቦ ምቤኪ የዓለም አቀፍ ጉዳዮች ኮሌጅ ውስጥ ተመራማሪ የሆኑት ራስ አድቮኬት ሲፎ ማንቱላ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ የቬንዙዌላን ጉዳይ ማዕከል አድርገን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አሁንም በሕግ የሚመራ ተቋም ነው—ወይስ ዓለም አቀፋዊ አስተዳደር የኃይል እና የመራጭነት (አድሏዊ) አፈጻጸም ጨዋታ ሆኗል? የሚለውን ጥያቄ በደቡብ አፍሪካዉ የታቦ ምቤኪ የዓለም አቀፍ ጉዳዮች ኮሌጅ ውስጥ ተመራማሪ ከሆኑት ከራስ አድቮኬት ሲፎ ማንቱላ ጋር በሰፊው እንመረምራለን። በተጨማሪም አንዳንድ አገራት ማዕቀብ ተጥሎባቸው ሕጋዊነታቸው እንዲታጣስ ሲደረግ፣ ሌሎች ደግሞ ጥበቃ የሚደረግላቸው ስለምንድን ነው? ይህስ በጂኦ-ፖለቲካዊ ሽኩቻ በተቀረጸው ዓለም ውስጥ ስለ ሉዓላዊነት ምን ይነግረናል? የሚሉትንም ጥያቄዎች እንዳስሳለን፡፡ በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ሙሉ መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

  25. 82

    ኢትዮጵያ፣ የእንቦጭ አረምን በአረንጓዴ አብዮት ጥቅም ላይ ማዋል

    "በጣና ሐይቅ ያለው የእንቦጭ አረም ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ስጋት ነው። ምክንያቱም ጣና ሐይቅ በላይኛው ጫፍ ላይ ስለሚገኝ ለግድቡ ተጽእኖ ይኖረዋል።" ሲሉ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የዓሳ ሀብትና የውሃ ሳይንስ ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር አያሌው ወንዴ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ ከዶ/ር የህዝቤ ካሳ፣ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ረዳት ፕሮፌሰር፣ ከአቶ ደበበ ደፈርሶ፣ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሃይድሮሎጂ እና የተፋሰስ መረጃ መሪ ሥራ አስፈፃሚ እና ከዶ/ር አያሌው ወንዴ፣ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የዓሳ ሀብትና የውሃ ሳይንስ ተመራማሪ ጋር በመሆን ኢትዮጵያ ወራሪውን የእንቦጭ አረምን በመዋጋት ረገድ እያደረገች ያለውን ትግል እንመረምራለን። ዶ/ር የህዝቤ በበኩላቸው ከእንቦጭ አረም ሊገኙ ስለሚችሉ እድሎች "ከእንቦጭ አረም የሚገኙ ባዮፈርቲላይዘሮችን መጠቀም በብዛት የሚገኝ ሲሆን ይህም በሰፊው ጥቅም ላይ ከዋለ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሊያደርግ ይችላል።" በማለት አክለዋል፡፡ በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ሙሉ መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

  26. 81

    አፍሪካ በወደቦች እና በኃይል መካከል፦ በባለብዙ-ዋልታ ዓለም ውስጥ ያለ ልማት እና ዲፕሎማሲ

    “ሩሲያ እ.ኤ.አ. እስከ 2027 ድረስ በአፍሪካ ውስጥ የኤምባሲዎቿን ቁጥር ወደ 49 አካባቢ ለማድረስ እየሠራች ነው። የሩሲያ ተዓማኒነትን በተመለከተ ከቅኝ ግዛት ታሪክ ነፃ መሆኗ ትልቁ ዲፕሎማሲያዊ ሀብት ታሪኳ ነው። እንደ ብሪታንያ፣ ፈረንሳይ ወይም ቤልጂየም ሳይሆን፣ የአፍሪካን ግዛቶች በቅኝ ግዛት አልገዙም። [...]ይህ ታሪክ ወደ “የእኩልነት አጋርነት” ትረካ የተቀየረ መሆኑ ነው፤ ይህም በተፈጥሮ ሀብታቸው፣ በወደፊት እጣ ፈንታቸው፣ በታሪካቸውና በውርሳቸው ላይ ሙሉ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለሚጥሩ አገራት ትልቅ ትርጉም የሚሰጥ ነው።” ሲሉ በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ መምህር የሆኑት አቶ መሀመድ ኢብራሂም ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህ ባለ ሁለት ክፍል የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ የጂቡቲን ኢኮኖሚያዊ እይታ እና ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ስትራቴጂያዊ ግንኙነት ከፍተኛ የፖሊሲ አማካሪ እና ኢኮኖሚስት ከሆኑት ከ ቆስጠንጢኖስ በርሄተስፋ(ዶ/ር) ጋር የተወያየን ሲሆን፤ በተጨማሪም፣ የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ዓመታዊ ጋዜጣዊ መግለጫን መሠረት በማድረግ፣ የአፍሪካን ሁኔታ በባለብዙ-ዋልታ ዓለም አቀፋዊ ምልከታ በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ መምህር ከሆኑት መሐመድ ኢብራሂም ጋር ዳስሰነዋል፡፡በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ሙሉ መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

  27. 80

    ዕዳን እንደ መሣሪያ፦ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓት አፍሪካን ጠፍሮ የያዘበት መንገድ

    “የእነዚህ ተቋማት (አይ.ኤም.ኤፍ እና የዓለም ባንክ ) መሠረታዊ ዳራ፣ ምን እንዲሠሩ ታስበው እንደነበር ወይም ምን እንዲያሳኩ ይጠበቅባቸው እንደነበረ በመነሳት ነው። እኔ እንደ አፍሮ-ሴንትሪስት (አፍሪካን ማዕከል እንደሚያደርግ ሰው)፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት የምዕራባውያንን የበላይነት ከሚያስፋፉ ወኪሎች ጋር ተመሳሳይ ናቸው የሚል ፍጹም የተለየ መከራከሪያ አለኝ። እነዚህ ተቋማት የተቋቋሙት ለአፍሪካ መልካም ጥቅም ነው የሚለውን መመሪያ በመቀበል፣ የምዕራባውያንን ብልሹነት ለማረጋገጥ በምናደርገው ጥረት በበላይነት ፖለቲካቸው ውስጥ ራሳችንን የምናስር ከሆነ፣ መዘንጋት የሌለብን ነገር ይሄ እርዳታ እንዳልነበረ ነው። ይህ በፋይናንስ በኩል የወረራ ተልእኳቸውን የበለጠ ለማስፋፋት የተደረገ ጥረት ነበር።” ሲሉ የ'ዲቨሎፒንግ አፍሪካ ? ኒው ሆራይዘን ዊዝ አፍሮሴንትሪክ' (Developing Africa? New Horizons with Afrocentricity) መጽሐፍ ደራሲ ሌሃሳ ሞሎይ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት የ ''Developing Africa? New Horizons with Afrocentricity'' መጽሐፍ ደራሲ ሌሃሳ ሞሎይ (ዶ/ር) ጋር ስለ አፍሪካ ዕዳ፣ እርዳታና ስለ ልማት የሚነገሩትን የተለመዱ ትርክቶች እንፈተሻለን።  ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ : 

  28. 79

    ሀገር በቀል ሳይንስ፦ የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ እና የወደፊቱ የእውቀት አመራር

    “የብሪክስ ሀገራት ተሰባስበው በብዙ ጉዳዮች ላይ እየተወያዩ ነው። የብሪክስ አካዳሚዎች ማህበር፣ የሳይንስ ማህበራት እና ሌሎችም አሉ። ይህ ደግሞ የበለጠ መቀጠል አለበት። አሁን ያለው ገና በጅማሮ ወይም በጨቅላነት ደረጃ ላይ ነው። ይህ ወደ ከፍተኛ ደረጃ ማደግ እና ወደ ተግባር መለወጥ ይኖርበታል።” ሲሉ ፕሮፌሰር ተከተል ዮሐንስ፣ የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ የኢትዮጵያን የሳይንስ እና የልማት ምኞቶች ቁልፍ ሚና የሚጫወተውን የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚን በትኩረት እንቃኛለን። የአካዳሚው ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ተከተል ዮሐንስ ፣ ተቋሙ ከኢትዮጵያ የራሷ ምሁራዊ መሰረት በመነሳት ምርምርን፣ ፈጠራን እና በማስረጃ ላይ የተመሰረተ የፖሊሲ ቀረፃን ለማጎልበት ስላለው ተልዕኮ እንወያያለን፡፡ በተጨማሪም አካዳሚው ሀገራዊ እድገትን እንዴት እየቀረጸ እንደሆነ፣ ከብሪክስ ሀገራት ጋር ያለውን ጨምሮ ዓለም አቀፍ አጋርነቶችን እንዴት እየገነባ እንደሆነ፣ እንዲሁም በግብርና፣ በአየር ንብረት መቋቋም፣ በትምህርት እና በሌሎችም ዘርፎች ላይ የሚያደርጋቸውን ለውጥ አምጭ እንቅስቃሴዎች እንቃኛለን። ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡

  29. 78

    ግብርና እንደ የኃይል ምንጭ፦ የአፍሪካ የግብርና ልማት ጥያቄዎች

    "የኢትዮጵያ የግብርና ምርት 94 በመቶው በጥሬው ነው ወደ ውጭ የሚላከው። ምንም ዓይነት እሴት አይጨመርበትም። [...] እኔ ማየት የምፈልገው አፍሪካ ራሷን መመገብ ብቻ ሳይሆን ለቀሪው ዓለምም ምግብ ስታቀርብ ነው። አፍሪካ ምግብ ለመግዛት በየዓመቱ ከ120 ቢሊዮን ዶላር በላይ እያወጣች መቀጠል የለባትም ስለዚህ ራሷን መመገብ ብቻ ሳይሆን ከዚያም በላይ የምትተርፍ አፍሪካን፤ በቂ የምግብ ምርት ለውጭ ገበያ የምትልክ አፍሪካን ማየት እፈልጋለሁ።" ሲሉ የግብርና ሳይንቲስት እና ተመራማሪ ፀደቀ አባተ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዚህ ባለ ሁለት ክፍል የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት በክፍል አንድ ከታዋቂው የግብርና ሳይንቲስት እና ተመራማሪ ከዶ/ር ፀደቀ አባተ ጋር በመሆን አፍሪካ ለምን ልማቷን ለሌላ አካል አሳልፋ መስጠት እንደማትችል፤ እንደ እንሰት ካሉ የሀገር በቀል ሰብሎች አንስቶ እስከ መሬት ፖሊሲ እና ሌሎች ጉዳዮች እንወያያለን። በክፍል ሁለት ደግሞ ኢትዮጵያ እንደ ኦፓል ያሉ ውድ ማዕድናትን በኢትዮጵያ ምርት ገበያ ለማካተት በምታደርገው እንቅስቃሴ ላይ በማተኮር፣ በማዕድን ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት ከብስራት ከበደ (ዶ/ር) ጋር በመሆን ዳስሰነዋል።  ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

  30. 77

    ከአንድነት ወደ ኃይል፦ በዓለም አቀፍ መድረክ የአፍሪካውያንን ተፅዕኖ የመገንባት ጉዞ

    "ጠንካራ የሆነ አለም አቀፍ የጥቁሮች ድርጅት ሊኖር ይገባል። ያለ እሱ፣ ሁሉም ነገር የቁጣ፣ የተቃውሞ እና የተስፋ መቁረጥ መግለጫ ብቻ ሆኖ ይቀራል። እኛ ጥቁር ህዝቦች ትኩረት ማድረግ ያለብን ገለልተኛ፣ አለም አቀፍ ተጽዕኖ ፈጣሪ እና ጠንካራ የሆኑ የጥቁር ተቋማትን በመገንባት ላይ መሆን አለበት።” ሲሉ የግሎባል ብላክ ሴንተር መስራች እና ዋና ፀሐፊ ከአቶ ፀጋዬ ቻማ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዛሬው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅታችን፣ ከግሎባል ብላክ ሴንተር መስራች እና ዋና ፀሐፊ ፀጋዬ ቻማ ጋር ስለ ፓን-አፍሪካኒዝም፣ ዓለም አቀፍ የካሳ ክፍያ እንዲሁም ተያያዥ ጉዳዮች እንወያያለን። በኢትዮጵያ ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ባለሙያ ይዘንጋው ይታየው ጋር የኢትዮጵያን አረንጓዴ የሽግግር ጉዞ እና ታዳሽ ኃይልን በተመለከተ ያደረግነው ውይይት ተካትቷል፡፡ እንዲሁም የተስፋ አዲስ ፓረንት ቻይልድሁድ ካንሰር ድርጅት ሥራ አስኪያጅ ሳራ ኢብራሂም፣ ስለ ሰብአዊ ትብብር፣ በኢትዮጵያ ስላለው የህፃናት ካንሰር ህክምና እና ድርጅታቸው ከሩሲያ ፌዴሬሽን ኤምባሲ ጋር ስላለው የረጅም ጊዜ አጋርነት ያጋሩንን ሀሳብ እናጋራችኋለን። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን  ያዳምጡ:

  31. 76

    የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት የዲጂታል ሽግግር፦"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" በተግባር

    "በኢትዮጵያ ፖስት ረገድ ላደንቀው የምፈልገው ነገር ቢኖር የአገልግሎት ምዝገባ ሂደቱን ነው። [...] የቨርቹዋል ሳጥን ተጠቃሚ ለመሆን የፋይዳ መታወቂያን መጠቀም ይቻላል፤ ከዚያም ሁሉም መረጃዎች ከፋይዳ ሥርዓት በቀጥታ ይሞላሉ። በመቀጠልም በተሳሰሩ የክፍያ መድረኮች አማካኝነት ክፍያ ይፈጸማል። በአንድ ወይም በሁለት ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የራሳችን የሆነ ቨርቹዋል ሳጥን እንዲኖረን ያስችለናል።" ሲሉ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አስተዳደር እና የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ባለሙያ አቶ እስክንድር መስፍን ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዛሬው የራይዚንግ ሳውዝ የሁለት ክፍል ዝግጅታችን፣ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አስተዳደር እና የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ባለሙያ ከሆኑት ከአቶ እስክንድር መስፍን ጋር በመሆን፣ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ጉልህ የዲጂታል ስራዎች ስለሆኑት "ቨርቹዋል የፖስታ ሳጥን" እና "ፖስት ገበያ" የምንወያይ ሲሆን፤ ከፌይዝ ምካችዋ (ደቡብ አፍሪካ)፣ ሪድሌይ ማካሊኪ ( የታዳሽ ኃይል ማዕከል) እና አቢዮላ አኪኖላ (ናይጄሪያ) ስለ ሃይል ሉዓላዊነት እና የቅኝ አገዛዝ ተፅዕኖን ማስወገድ በተመለከተ በሁለተኛው የዝግጅታችን ክፍል እናስደምጣችኋለን፡፡ ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡

  32. 75

    የኦንላይን እና ርቀት ትምህርት በኢትዮጵያ፣ ዕድል እና ተግዳሮት

    “አንድ ሀገር ማደግ፣ መለወጥ፣ መበልጸግ ካለባት በተማሩ ዜጎቿ ነው የሚወሰነው። አንድ ሀገር ዲሞክራቲክ ለመሆን ካስፈለጋት በተማሩ ዜጎቿን ነው የሚወሰነው። ያልተማረ ህብረተሰብ በፈለከው መስመር ልትነዳው፣ በፈለከው ጊዜ የፈለከውን ነገር ልጭንበት ትችላለህ።” በኦንላይን እና ርቀት ትምህርት ዘርፍ ተመራማሪ ረ/ፕ አደራጀው ተሰማ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ በኢትዮጵያ ያለውን በኦንላይን እና ርቀት ትምህርት ዘርፍ ተመራማሪ ከሆኑት ከረ/ፕ አደራጀው ተሰማ (ዶ/ር) በመሆን የዲጂታሉ ዓለም እየተፋጠነ ባለበት በዚህ ወቅት፣ ኢትዮጵያ ወጥ ካልሆነ የኢንተርኔት ተደራሽነት፣ የመሠረተ ልማት ክፍተቶች እና ውስን ከተቋማዊ ዝግጁነት ጋር ተያይዞ የሚመጣ ውስብስብ እውነታ ተደቅኖባታል። በኢትዮጵያ የኦንላይን እና ርቀት ትምህርት ዘርፍ በአሁኑ ወቅት ውጤታማ የሆኑትን ነገሮች፣ ሥርዓቱ ክፍተት ያለባቸውን ነጥቦች እና የዲጂታል ትምህርት ጥቂት ዕድሉ ያላቸውን ብቻ ሳይሆን ሁሉንም ተማሪዎች እንዲያገለግል ምን መለወጥ እንዳለበት ውይይት አድርገናል። በተጨማሪም የኦንላይን እና ርቀት ትምህርት ዕውቀትን ለሁሉም ለማዳረስ የሚረዳ መሣሪያ ነው ወይስ በከተማ እና በገጠር ማህበረሰቦች መካከል ያለውን ልዩነት የሚያሰፋ? የሚለውን እና ተያያዥ ጉዳዮችን እንዳስሳለን፡፡

  33. 74

    አእምሮአዊ ሉዓላዊነት፦ በአፍሪካ እውቀትን የሚቆጣጠረው ማን ነው?

    "ራሴን እንደ ምሁር ሳይሆን በህብረተሰቡ ውስጥ እንደ ተማሪ አድርጌ ባስቀመጥኩባቸው ጊዜያት ሁሉ፣ በቋንቋዎቻችን ውስጥ ያለውን ጥልቅ የፍልስፍና ይዘት ይበልጥ ለመረዳት ችያለሁ።[…]ሰዎች ባሉበት ሁሉ አስተሳሰብ አለ፤ አስተሳሰብ ባለበት ሁሉ እውቀት አለ፤ እውቀት ባለበት ሁሉ ደግሞ ፍልስፍና አለ፡፡” ሲሉ በደቡብ አፍሪካ ዩኒቭርስቲ /ዩኒሳ/ መምህርት ፕ/ር ሻባላኒ ኖኩቱላ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በአእምሮአዊ ሉዓላዊነት እና የአፍሪካን ትምህርት ከቅኝ ግዛት ተጽዕኖ ነፃ ስለማውጣት በሚመለከት ከፕ/ር ሻባናኒ ኖኩቱላ ጋር አፍሪካ የፖለቲካ ነፃነት ብታገኝም፣ ብዙ የአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች አሁንም የአፍሪካን ታሪክ፣ ቋንቋዎች እና የእውቀት ሥርዓቶች ወደ ጎን በሚገፉ የቅኝ ግዛት ዘመን መዋቅሮች ውስጥ እየሰሩ ስለሚገኙበት ምክንያት፣ እነዚህ ውርሶች እንዴት እንደቀጠሉ እና መቀየር ስለሚቻልባቸው መንገዶች እንወያያለን፡፡ “ምናልባትም የ21ኛው ክ/ዘመን 'መሃይም' ተብለው የሚጠሩት ማንበብና መጻፍ የማይችሉት ሳይሆኑ፤ የተሳሳቱ እውቀቶችን መተው እና አዳዲስ እውቀቶችን መልሶ መማር የማይችሉት ናቸው።" በማለትም ፕሮፌሰር ሻባላኒ አክለዋል፡፡ ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን  ያዳምጡ:

  34. 73

    ''ቅድሚያ ለአሜሪካ የጤና ስምምነት'':- ለአፍሪካ አጋርነት፣ ጉልበት ወይስ ጥገኝነት?

    "[የአፍሪካ] መንግስታት ከሲቪል ማህበረሰብ፣ ከሰብዓዊ መብት ተሟጋች ቡድኖች እና ከሌሎች አካላት ጋር ቢመክሩ ኖሮ፣ ከእነዚህ ቡድኖች ሊመጣ በሚችለው ጫና ምክንያት መንግስታቱ ወደ ስምምነቱ ላይገፉ ይችሉ ነበር። በአሁኑ ወቅት ከኬንያ እያየን ያለነው በጣም የሚደነቅ ነገር ቢኖር ጠንካራ የሲቪል ማህበረሰብ ንቅናቄ መኖሩን ነው፤ ወደ 50 የሚጠጉ ድርጅቶች አሁን ያለውን ስምምነት በመቃወም መቆማቸው የስምምነቱን የተወሰነ ክፍል ለማስቆም አስችሏል።" ሲሉ በደቡብ አፍሪካ የሚግኙት የማህበረሰብ ጤና ባለሙያ የሆኑት ዶ/ር ሻኪራ ቹናራ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዛሬው ልዩ የራይዚንግ ሳውዝ የሁለት ክፍል ዝግጅታችን፣ የአፍሪካን የጤና ሉዓላዊነት እና የፈጠራ አድማስ እንቃኛለን። በመጀመሪያው ክፍል፣ ከዶ/ር ሻኪራ ቹናራ ጋር በመሆን ቅድሚያ ለአሜሪካ የጤና ስምምነት የተሰኙ የጤና ስምምነቶች ያላቸውን አንድምታ በመተንተን፣ ከአፍሪካ የጤና እና የዘረመል መረጃዎች (ጂኖሚክ ዳታ) ትክክለኛ ተጠቃሚ ማን እንደሆነ እንዲሁም በዚህ ስምምነት ምክንያት የአፍሪካ ሀገራት እንዴት ባለ መልኩ ዘላቂ ጉዳት ሊደርስባቸው እንደሚችል የሚያስረዱ ሲሆን፤ በመቀጠል፣ ኢትዮጵያዊው የቴክኖሎጂ ስራ ፈጣሪ ጆኤል ጣልአርጌ አፍሪካውያን የፈጠራ ባለሙያዎች እንዴት የአካባቢውን ሀሳቦች ወደ ተጨባጭ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ መቀየር እንደሚችሉ ያካፍለናል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

  35. 72

    ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030፦ የኢትዮጵያ የዲጂታል ሽግግር ጉዞ

    “እኛ [ኢትዮጵያውዊያን] በከፍተኛ ሁኔታ ከውጭ በሚገቡ የዲጂታል ሀብቶች ላይ ጥገኛ ነን። ስለዚህ ውይይታችን ስልታዊ እስከሆነ ድረስ እኔ የምመክረው የራሳችን የሆነ የመረጃ ሉዓላዊነት እንዲኖረን ነው። የመረጃ ሉዓላዊነትን የሚያበረታታ እና የሚሟገት የመረጃ አስተዳደር ፖሊሲ ሊኖረን ይገባል። [ለዚህም] በኢትዮጵያ ውስጥ የመረጃ ኤምባሲዎችን ማቋቋም ያስፈልገናል።” ሲሉ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አስተዳደርና ስትራቴጂ ባለሙያ እስክንድር መስፍን ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት የመጀመሪያው ክፍል የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አስተዳደርና ስትራቴጂ ባለሙያው እስክንድር መስፍን፣ ታህሳስ 11 ይፋ የሆነውን “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” ስትራቴጂ ያብራራሉ። ስትራቴጂው በዲጂታል ክፍያ፣ በሳይበር ደህንነት፣ እና በቀጣናዊ ዲጂታል ውህደት ዙሪያ ያለውን ሚና ከኢትዮጵያ የብሪክስ አባልነት ጋር የተያያዙ ዕድሎችን ጨምሮ ይዳስሳሉ። በሁለተኛው ክፍልም በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የሐዲስ ዓለማየሁ የባህል ጥናት ተቋም ዳይሬክተር ወንድይፍራው ምህረት(ዶ/ር) ጋር ሀገር በቀል እውቀት መልሶ ማግኘት ለጤና እና ለዘላቂ ልማት ለምን አስፈላጊ ሆነ ስንል እንፈትሻለን። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን  ያዳምጡ:

  36. 71

    የሆሊውድ የባህል ወረራ ፦ አፍሪካዊ ማንነቶች ላይ ያነጣጠረው አዲስ የቅኝ ግዛት መልክ

    “የሆሊውድ ተጽእኖ ምንም ጥርጥር የለውም፤ ከፍተኛ ተጽእኖ አለው፤ ጉዳቱ ያመዝናል ግን ቢሆንም ጠቃሚነቱም ደግሞ የሚካድ አይደለም። [...] ምዕራባውያን በአብዛኛው ፊልሞቻቸው ላይ የበላይነታቸውን ሊያሳዩን ይሞክራሉ፡፡ [...] በተቃራኒው ደግሞ የአፍሪካን ኋላቀርነት እና አስከፊ ገጽታ ለመገንባት ይሞክራሉ፤ ይህም ትውልዱ ራሱን እና ሀገሩን የሚያይበትን መንገድ የተበላሸ እንዲሆን ያደርጋሉ፡፡” ሲል ደራሲ ፣ ዳይሬክተርና ተዋናይ ቢኒያም ወርቁ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግሯል፡፡በዚህኛው ባለሁለት ክፍል የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል፣ የፊልም እና ቲያትር ባለሙያ ከሆነው ከደራሲ ፣ ዳይሬክተርና ተዋናይ ቢኒያም ወርቁ ጋር በመሆን የምእራብያውያን የፊልም እና ሌሎች የጥበብ ስራዎች ቀሪውን ዓለም የሚቃኙበት እና የሚያቀርቡበት መንገድ እንዴት ባለ መልኩ ተጽዕኖ እየፈጠረ እንዳለ ባለሙያዎች ይህን የባህል ወረራ እንዴት ባለ መልኩ መመከት እንደሚችሉ በሰፊው ቃኝተናል፡፡ በኬንያ እና በሴኔጋል መካከል የተፈረመውን ከቪዛ ነጻ እንቅሳቃሴን መሰረት በማድረግ ይህ ለአፍሪካ እና አፍሪካውያን የሚኖረው ትርጉም፣ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው፣ እንዲሁም ከአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ዓላማ ጋር የሚኖረውን መጣጣም የፓን አፍሪካኒዝም አቀንቃኝ፣ ደራሲ እንዲሁም የቱሪዝም ባለሙያ እና የባህል ጉዳዮች አንቂ ራስ አብይ ጥላሁን ጋር ያደረግነው ቆይታም በሁለተኛው የዝግጅታችን ክፍል ተዳስሷል፡፡ ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡

  37. 70

    አህጉራዊ ፅናትን መገንባት፦ የሩሲያ–አፍሪካ ትብብር ሚና በግብርናው ዘርፍ

    "እያንዳንዱ ማህበረሰብ የራሱ የሆነ ጥበብ እና የራሱ የሆኑ ሀብቶች አሉት። በሚያሳዝን ሁኔታ ግን፣ ማህበረሰቦች እነዚህን ጥበቦች፣ ሀብቶች እና መሣሪያዎች በመደበኛው የትምህርት ሥርዓት ውስጥ ምን ያህል አካተውታል የሚለው ጉዳይ፣ በእኛ ላይ ተጽዕኖ ከማሳደሩም በላይ አሁን ላለንበት የልማት ደረጃ የራሱን አስተዋጽኦ ያበረክታል።" ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ጤና ትምህርት ቤት ባለሙያ እና ተመራማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር ሚርጊሳ ካባ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ባለ ሁለት ክፍል ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ኮሌጅ ዲን ከሆኑት ዘሪሁን ደምረው (ዶ/ር) ጋር በመሆን በካይሮ በተካሄደው የሁለተኛው የሩሲያ–አፍሪካ የሚኒስትሮች ጉባኤ ላይ የግብርና ዘርፍ ትብብርን አስመልክቶ በሰፊው ተወያይተናል፡፡  ሁለተኛው ክፍልም ትኩረታችንን  የሀገር በቀል እውቀቶችን በትምህርት እና በጤና ሥርዓቶች ውስጥ ስለማቀናጀት አድርገን  በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የአንኮበር የዕፅዋት ሕክምና ፕሮጀክት አስተባባሪ ዶ/ር አማረ አያሌው፣ የማህበረሰብ ጤና ባለሙያ እና የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከፍተኛ አማካሪ ፕሮፌሰር መንገሻ አድማሱ እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ጤና ትምህርት ቤት ባለሙያ እና ተመራማሪ ፕሮፌሰር ሚርጊሳ ካባ ትምህርትን ከቅኝ ግዛት አስተሳሰብ ነፃ ማውጣት፣ የሀገር በቀል ሕክምናን ሚና ተያያዥ ነጥቦች ላይ ሀሳባቸውን አካፍለውናል፡፡ ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን  ያዳምጡ:

  38. 69

    የሩሲያ - አፍሪካ ግንኙነት ፦ አዳዲስ አድማሶች፣ ነባር ወዳጆች

    "በበርካታ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ሰላም በመጥፋቱ እንጨነቃለን፤ ምክንያቱም በአፍሪካ አህጉር ስለ ብልጽግና ማውራት የምንችለው ሰላም ሲኖር ብቻ ነው ብለን እናምናለን። ሰላም ካለ 'የምንመኛት አፍሪካ' ወደተሰኘው የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ-2063 ግቦች ለመድረስ መስራት እንችላለን። እንደ ሩሲያ ያሉ ሀገራት ለዓመታት ያካበቱትን ልምድና አቅም በመጠቀም የተሻለች ዓለምን መገንባት እንደምንችል እናምናለን።" ሲሉ የቦትስዋና የዓለም አቀፍ ግኑኝነት ሚኒስትር ፌንዮ ቡታሌ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል የቦትስዋና የዓለም አቀፍ ግኑኝነት ሚኒስትር የሆኑት ፌንዮ ቡታሌ (ዶ/ር) እና አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በካይሮ የተካሄደውን ሁለተኛው የሩሲያ-አፍሪካ የሚኒስትሮች ኮንፈረንስ አስመልክቶ ስለ ትብብር፣ የእጅአዙር ቅኝ ግዛት ፣ ስለ ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) እና ተያያዥ ጉዳዮች ሃሳባቸውን አጋርተውናል፤ በዝግጅታችን ሁለተኛው ክፍልም “የዓመቱ ማጠቃለያ ከቭላድሚር ፑቲን ጋር” የተሰኘውን ዓመታዊ ፕሮግራምን መሰረት በማድረግ በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ የውጭ ፖሊሲ እና ዲፕሎማሲ መምህር እና ተመራማሪ አበራ ሄጲሶ ጋር በመሆን በፕሮግራሙ ስለተነሱት አንኳር ነጥቦች ውይይት አድረገናል፡፡ ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ 

  39. 68

    ደቡባዊው ዓለም በእንቅስቃሴ ላይ፦ ኢትዮጵያ ፣ ብሪክስ እና የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ትግል

    "የብሪክስ አገራት አንዱ ስምምነት በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በምርምር እና በፈጠራ፣ እንዲሁም በተለያዩ የፋርማሲዩቲካል እና የሕክምና መሣሪያዎች ጉዳዮች ላይ በጋራ መሥራት ነው። ይህም ከስኳር እና ከሌሎች መሰል ልማዳዊ አሠራሮች ወደ ከፍተኛ የቴክኖሎጂ ፈጠራ እና ተሳትፎ ለመሸጋገር ያስችላል። ምክንያቱም የብሪክስ መመሪያዎች፣ ስምምነቶች እና ፍላጎቶች ከነዚህ መሰል ልማዳዊ አሠራሮች ወደ ከፍተኛ ቴክኖሎጂዎች በመሸጋገር በእስያ እንዲሁም በአፍሪካ አገራት፣ በተለይም በኢትዮጵያ፣ ምርትን እና ምርታማነትን ማሳደግ ነው" ሲሉ በወራቤ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ መምህር የሆኑት መሐመድ ሙሳ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።  በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ባለ ሁለት ክፍል ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል የወራቤ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ መምህር ከሆኑት ከዶ/ር መሐመድ ኢሳ ጋር ኢትዮጵያ በብሪክስ ውስጥ እራሷን እንዴት እያዘጋጀች እንደሆነ እና በተለይም የህንድ ሚና ላይ ትኩረት በማድረግ የተወያየን ሲሆን፤ በኢትዮጵያ የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት  ጀማል መሐመድ(ዶ/ር) የገቢ ምርቶችን በአገር ውስጥ ምርቶች ስለመተካት በጥልቀት የሰጡት ትንታኔ በሁለተኛው ክፍል ተካትቷል፡፡ ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ :

  40. 67

    የታሪክ ባለቤትነት እና የይዞታ ባለቤትነትና ፍትሕ በአፍሪካ

    “ዓላማችን መሆን ያለበት የአፍሪካ ወጣቶችን አእምሮ ከቅኝ ግዛት አስተሳሰብ ነፃ ማውጣት ነው፤ ምክንያቱም ባለፉት ጥቂት መቶ ዓመታት የአፍሪካ ታሪክ ሲታጠብና ሲበረዝ ቆይቷል። [...]ስለሆነም፣ አሁን ባለው የግዙፍ የሃሳብ ለውጥ ወቅት፣ ታሪካችን ከአፍሪካ ነፃነት ጋር እንዳልተጀመረ በአፍሪካም ሆነ በመላው ዓለም ለሚገኙ ወጣቶች የማሳወቅ፣ የማስተማር እና ግንዛቤ የመፍጠር ኃላፊነት የኛ ነው።” ሲሉ የቱሪዝም ባለሙያ እና የባህል ጉዳዮች አንቂ ራስ አብይ ጥላሁን ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህኛው ባለሁለት ክፍል የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል፣ የቱሪዝም ባለሙያ እና የባህል ጉዳዮች አንቂ ራስ አብይ ጥላሁን አፍሪካውያን ቅርሶቻቸውን እና ግዛቶቻቸውን ለንግድ መጠቀሚያ ከሚያደርጉ ሥርዓቶች ታሪካቸውን እንዴት መልሰው እየተረከቡ እንደሆነ እንዲሁም ስለ አፍሪካ አንድነት፣ ስለ ታሪካዊ ንቃት እና ባህልን ማዛባት ስለሚያስከትለው አደጋ በሰፊው ተወያይተናል፡፡ በሁለተኛው ክፍል ደግሞ፣ ከታሪክ ባለቤትነት ወደ መሬት ፍትሕ ተሻግረን ስላልተቋጨው የአፍሪካ የመሬት ባለቤትነት እና የሉዓላዊነት ትግል ከደቡብ አፍሪካ የመሬት ማሻሻያ እና የገጠር ልማት ሚኒስትር ምዝዋኔሌ ኞትሶ፣ የዚምባብዌ መሬት ኮሚሽን ሰብሳቢ ቴንዳይ ሩት ዎከር እና የክዋሜ ንክሩማ ዩኒቨርሲው ፕሮፌሰር ሩዲዝ ኪንግ ጋር ቆይታ እናደርጋለን። ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

  41. 66

    በርሊን ኮንፈረንስ፡-የምዕራባውያን ኢ-ፍትሐዊነት እና በደል በአፍካውያን ላይ

    “አፍሪካውያን ሸማቾች እንዲሆኑ፣ ከዛ በፊት አይተው የማያውቁትን የአውሮፓ እቃ መሸመት፣ መጠቀም እንዲችሉ ብዙ ተዘዋዋሪ መንገዶችን ይጠቀማሉ። አፍሪካውያን ያለነዛ ሽቀጦች ህይወታቸውን መምራት እንዳይችሉ አድርገው አጣብቂኝ ውስጥ ይከቷቸዋል።” ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህርና ተመራማሪ ደቻሳ አበበ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ባለ ሁለት ክፍል ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል፣ የአውሮፓ ወራሪ ኃይሎች በበርሊን ኮንፈረንስ ላይ ያደረጉት አፍሪካን የመቀራመት ስምምነት በአፍሪካ እና አፍሪካውያን ላይ ስላንጸባረቁት ኢ-ፍትሐዊነት እና ስላደረሱት በደል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህርና ተመራማሪ ከሆኑት ደቻሳ አበበ (ዶ/ር) ጋር በመሆን እንዳስሳለን፡፡ የኢትዮጵያ የበቆሎ ምርት ያለበትን ደረጃ እና በቆሎ የሀገሪቱን የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ አንጻር ስላለው ሚና በበቆሎ ሰብል ላይ ተመራማሪ ቢተው ጥላሁን (ዶ/ር) ጋር ያደረግነው ውይይትም በሁለተኛው ክፍል ይዳሰሳል፡፡ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

  42. 65

    አፍሪካን ከውስጥ ወደ ውጭ መገንባት፡ ባህል፣ ገንዘብ (ምንዛሪ) እና የኃይል ትስስር

    “በእኛ የሥነ ምግባር እሴቶች ላይ በመመሥረት፣ ለህብረተሰቦቻችንና ለኅብረተሰባችን ጥሩ የሆነውንና አስፈላጊ የሆነውን ነገር መከላከል አለብን። በትክክለኛ መረጃ እና በተገቢው ግንኙነት በትክክል መከላከል አለብን። […]የመንግሥት መዋቅር በሽማግሌዎች ላይ እምነት ሊኖረውና ሥልጣንን በአግባቡ መወከል አለበት፤ ዝም ብሎ በስም ብቻ ሳይሆን።” ሲሉ የኢትዮጵያ የሽማግሌዎች ምክር ቤት ሊቀመንበር የሆኑትተስፋጽዮን ደለለው(ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ባለ ሦስት ክፍል ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል የኢትዮጵያ የሽማግሌዎች ምክር ቤት ሊቀመንበር የሆኑትተስፋጽዮን ደለለው(ዶ/ር) ጋር ባህላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓቶች ሰላምን መገንባትና ማንነትን መጠበቅበተመለከተ ሚናቸውን እንቃኛለን፡፡ በሁለተኛውም ክፍል ደግሞ የፓን-አፍሪካ የክፍያ ሥርዓትና እያደገ የመጣውን የኢትዮጵያን የዲጂታል ፋይናንስ ስትራቴጂ ተስፋዎችን ለአፍሪካ የፋይናንስ ሉዓላዊነት ያላቸውን ሚና እንቃኛለን፡፡ በመጨረሻውም ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ዘርፍ በተገኙ ግንዛቤዎች የአፍሪካን የኃይል ተቃርኖ እንመረምራለን ለዚህም በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አገልገሎት የ 'ኤኤምአይና ስካዳ' ሥራ አስኪያጅ ከአቶ ዘሪሁን አበበ ጋር ባደረነው ውይይት ዳስሰነዋል፡፡ ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

  43. 64

    ያልታየና ያልተነገረ፡ የካንሰር በሽታ በኢትዮጵያ

    “በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ80,000 ሰዎች በላይ አዳዲስ የካንሰር በሽታ ይያዛሉ። ከእነዚያ ከ80,000 ኬዞች መካከል ደግሞ 54,000 ያህሉ በዚያው ዓመት ህይወታቸው ያልፋል […] ከኤች አይ ቪ፣ ቲቢ እና ወባ ጋር ሲነጻጸር የካንሰር ሞት መጠን ከሦስቱ በሽታዎች ጥምር ይበልጣል።” ሲሉ የካንሰር ኤፒዲሚዮሎጂስት፣ የስታቲስቲክስ ባለሙያ እና የአዲስ አበባ ከተማ ካንሰር ምዝገባ ሥራ አስኪያጅ ሰለሞን አስማረ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ የኢትዮጵያን እየጨመረ የመጣውን የካንሰር ጫና ከባለሙያ እንመረምራለን። ብዙ የካንሰር ኬዞች በጣም ዘግይተው የሚታወቁት ለምንድን ነው? ማዕበሉን ለመቀየር ምን መደረግ አለበት? እና ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ከካንሰር ኤፒዲሚዮሎጂስት፣ የስታቲስቲክስ ባለሙያ እና የአዲስ አበባ ከተማ ካንሰር ምዝገባ ሥራ አስኪያጅ ሰለሞን አስማረ ጋር ጥልቅ ውይይት አድርገናል፡፡ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

  44. 63

    የውጭ እርዳታ መቀነስ፡ በኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ ላይ ተስፋና ስጋት

    “የውጭ እርዳታ ማጣት በጣም አሳሳቢ ጉዳይ ነው […] ለቲቢ፣ ኤች አይ ቪ እና ወባ አስፈላጊ የሆኑ መድኃኒቶችን ግዥ ያለ እርዳታው በተግባር የማይቻል ነው። ነገር ግን አርቀን ስንመለከት ይህ የማንቂያ ደወል ሊሆን ይችላል። ለአፍሪካ ለቲቢ፣ ኤች አይ ቪ ወይም ጤና ብቻ ሳይሆን ለእርሻ፣ ትምህርት እና ሌሎችም ሀብትን በማሰባሰብ በራሷ ላይ ለመደገፍ ጥሩ አጋጣሚ ሊሆን ይችላል።” ሲሉ የ'ቮለንተሪ ሄልዝ ሰርቪስ' ኢትዮጵያ መስራችና ዋና ዳይሬክተር እንዳልካቸው ፍቃዱ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡  በቲቢ በሽታ ከፍተኛ ጫና ካለባቸው አገሮች መካከል የሆነችው ኢትዮጵያ የጤና አጠባበቅ ሥርዓቷ ዋነኛ የጀርባ አጥንት የነበረው የውጭ እርዳታ እየቀነሰ በመምጣቱ ወሳኝ ወቅት ላይ ትገኛለች። ዓለም አቀፍ የገንዘብ ድጋፍ መቀነስ የቲቢ ቁጥጥር ጥረቶችን ማለትም ምርመራን፣ ሕክምናን እና የመድኃኒት መቋቋምን አደጋ ላይ እየጣለ ነው።  በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት ከ'ቮለንተሪ ሄልዝ ሰርቪስ' ኢትዮጵያ መስራችና ዋና ዳይሬክተር እንዳልካቸው ፍቃዱ ጋር በመሆን የጤና በጀት ቅነሳ በኢትዮጵያ የሳንባ ነቀርሳ ህክምና ላይ የሚያሳድረውን ተጨባጭ ተፅዕኖ ዳስሰናል።ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

  45. 62

    ኢትዮጵያዊው ጠበቃ የህግ የበላይነት ተጋድሎ፡ የምሥራቅና ደቡብ አፍሪካ የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) ክስ ጉዳይ

    “ይህ ክስ ለመላው አህጉር ታላቅ ምሳሌ የሚሆን የሕግ መሠረት መጣል የቻለ ነው። […] በአኅጉራዊና ክልላዊ አካላት ውስጥ ያሉ አንዳንድ ባለሥልጣናት ውሳኔያቸው የማይነኩ እና የማይጠየቁ እንደሆኑ ሊያስቡ ይችላሉ። ነገር ግን መጠየቅ አለበት። እናም፣ በዚህ ዓይነት ክስ የሚጠቀሙት የመጀመሪያው አካል ክሱን ያቀረበው ግለሰብ ሳይሆን፣ ተቋሙ ራሱ ነው።” ሲሉ የፓን አፍሪካ ህግ ባለሙያዎች ህብረት እና የኢትዮጵያ የጠበቆች ማኅበር ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ጌታቸው ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ባለ ሁለት ክፍል ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል የፓን አፍሪካ ህግ ባለሙያዎች ህብረት እና የኢትዮጵያ የጠበቆች ማኅበር ፕሬዚዳንት ከሆኑት ከአቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው ጋር በመሆን በምሥራቅና ደቡብ አፍሪካ የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) የፍትህ ፍርድ ቤት ያገኙትን ታሪካዊ ድል — በተመለከተ የተወያየን ሲሆን፤ የ2025 የአፍሪካ ሴት የመገናኛ ብዙኃን ዘጠነኛ ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ተገኝተን የሴቶችን ውክልና፣ በአፍሪካ ውስጥ ደህንነቱ የተጠበቀና ሁሉን ያካተተ የሚዲያ ምህዳር መገንባትን በተመለከተ ከዶ/ር የሚሲ አኪንቦቦላ፣ ጆይ አዲግዌ እና ማሪያማ ባህ ጋር ያደረነው ቆይታ በሁለተኛው የዝግጅታችን ክፍል ተዳስሷል፡፡ ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡

  46. 61

    የሐይማኖታዊ እና ባህላዊ እሴቶች ሚና ጾታን ጥቃቶችን ለመከላከል

    “የመጀመሪያው ትልቁ ነገር የሰውን ልጅ ክብር ማሳወቅ ነው። የሰው ልጅ ክብር፣ አንዱ ጉልበት ስላለው ሌላውን ጉልበት የሌለውን የማጥቃት መብት እንዳለው ተደርጎ የሚቆጠርበት አለመሆኑን፣ ሰውን ማክበርን ፈጣሪን መፍራትን፣ ህግን መጠበቅን በተለይ ደግሞ አጥቂነትን፣ የአጥቂነት ባህሪን በተቻለ መጠን አውግዞ በማስተማር የሀይማኖት ተቋማት ትልቅ ድርሻ አላቸው።” ሲሉ በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የስነመለኮት መምህር የሆኑት መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ባለ ሁለት ክፍል ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው ጾታን መሰረት ስላደረገ ጥቃት እንዲሁም በመንግስት እና በሃይማኖት ተቋሟት በኩል መደረግ ስለሚገባቸው የተለያዩ ተግባራት በሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር የሴቶች መብት ጥበቃና ምላሽ መሪ ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ዘካሪያስ ደሳለኝን፣ የህግ ባለሙያ እና የሴቶችን አቅም ማጎልበት ባልሙያ የሆኑትን ወ/ሮ ቤተልሄም ድጉን እንዲሁም በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የስነመለኮት መምህር የሆኑት መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል ያነጋገርናቸው ሲሆን፤ ቻይና በኤሌክትሪክ መኪኖች ሽያጭ ላይ ያወጣቸው ጥብቅ ፖሊሲን ተከትሎ በኢትዮጵያ ላይ ሊፈጥር የሚችለውን ጫና በኤሌክትሪክ መኪኖች ዙሪያ በማማከር ከሚታወቁት ከአቶ ብሩክ አወቀ ጋር ያደረግነው ውይይት በሁለተኛው የመሰናዶኣችን ክፍል ተካትቷል፡፡  ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ :

  47. 60

    ትምህርትና ሉዓላዊነት ፡- የአፍሪካ የመምህራን ሥልጠናን ከቅኝ ግዛት ጥላ ነጻ መውጣት

    “ቀጥታ የውጭውን ዓለም የሥርዓተ ትምህርት ከኢትዮጵያውያን ህይወት ጋር ብዙም ግንኙነት የሌለው፣ ልጆቹን ትራንስፎርም የማያደርግ፣ አካባቢውን የማይለውጥ፣ አካባቢውን ያልተገነዘበ ሥርዓተ ትምህርት ታመጣና [...] ኢትዮጵያ አምጥተህ ስታስቀምጠው አይገጣጠምም፡፡” በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋ እና የትምህርት ኮሌጅ የሳይንስ ትምህርት ረዳት ፕሮፌሰር እና በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት አማካሪ ምክር ቤት አባል ሰለሞን በላይ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት ላይ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋ እና የትምህርት ኮሌጅ የሳይንስ ትምህርት ረዳት ፕሮፌሰር እንዲሁም በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት አማካሪ ምክር ቤት አባለ ከሆኑት ከሰለሞን በላይ (ዶ/ር) ጋር የመምህራን ትምህርትን ከቅኝ አገዛዝ ነፃ ማድረግ ምን ማለት እንደሆነ፤ ይህም የአፍሪካን ጥበብ፣ ባህል እና ማንነት ወደ ትምህርት ዋና ማዕከል መመለስ እንዴት እንደሚቻል፤ እንዲሁም አፍሪካ የትምህርት ሥርዓቷን የራሷን እውነታዎች እንዲያንፀባርቁ አድርጋ ዳግም እንዴት ልትቀርጽ ትችላለች? የሚሉና ተያያዥ ጉዳዮች የተንሱበትን ይህን መሰናዶ ይከታተሉ። ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

  48. 59

    አማራጭ ሀብት ለአፍሪካ ዕድገት፡ ከባህላዊ የኢንቨስትመንት መንገዶች ባሻገር

    “የአማራጭ ሀብቶች ፣ ለምሳሌ የሰው ካፒታል መረጃ ጠቋሚ ምርታማነት፣ የህዝቡ መጠን እና የኢኮኖሚዎ ስፋት—ተቋማዊ ሁኔታዎችንሊቀይሩ/ሊያስተካክሉ ይችላሉ። ስለዚህ፣ አማራጭ ሀብቶች ልክ እንደ ቀጥተኛ የውጭ ኢንቨስትመንት በተመሳሳይ መንገድ ተጽዕኖ አያድርባቸውም፡፡” ሲሉ የማኔጅመንትና ኢኮኖሚክስ አማካሪ ሳታ አብርሃም (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ባለ ሁለት ክፍል ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል ከሰሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ ሀገራት በአማራጭ ሀብት ላይ ከሚሰሩ ቀደምት ተመራማሪዎች አንዱ ከሆኑት ሳታ አብርሃም (ዶ/ር) ጋር በመሆን ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ወስጥ የግል ሀብት ፣ ቬንቸር ካፒታል ፣ መሰረተ-ልማት ፣ እና ቋሚ ንብረቶች ኢንቨስትመንት ዙሪያ ያለውን ለውጥ እና እውነታ የምንዳስስ ሲሆን፤ በሁለተኛው የዝግጅታችን ክፍል ደግሞ በመጀመሪያው የአፍሪካ ኅብረት የዲጂታል ግብርና ጉባኤ ላይ ተገኝተን በአፍሪካ ውስጥ በግብርና ሥራ ፈጣራ ላይ ከተሰማሩት ከዶ/ር ኢንግሪድ ኤፓዛኝ፣ ፑሪቲ ኤኮህ-ኦዴቺኩ እና ባላቂስ ሰላውዲን ኢብራሂም ጋር ስለ ዲጂታል ግብርና ያደረግነው ውይይት ተካትቷል፡፡ ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ

  49. 58

    የማካካሻ ፍትህ ፦ ለአፍሪካ ለምን አስፈላጊና ወሳኝ ጥያቄ ሆነ ?

    “የቅኝ ግዛት ካሳ ጉዳይ ማንሳት ከታሪካዊ እይታ አንጻር ብቻ ሳይሆን ከፖለቲካዊና ከሥነ-ልቦናዊ እይታ አንጻርም ጭምር በጣም አስፈላጊ ነው። ይህም አሁን ያለው የምዕራቡ ዓለም ትውልድ እንዲሁም አሁን በአፍሪካ እና በሌሎች በዓለም ዙሪያ በሚገኙ የቅኝ ግዛት ሥር በነበሩ አገሮች የሚኖሩት ትውልዶች በእነዚህ አካባቢዎች ጭቆና፣ ብዝበዛ እና አሰቃቂ የቅኝ ግዛት አገዛዝ እንደነበረ ማወቅ አለባቸው።” ሲሉ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁሩ ዳዊት መዝገበ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ባለ ሁለት ክፍል ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁሩ ዳዊት መዝገበ፣ የቅኝ ግዛት ካሳ ለአፍሪካ ክብር፣ ሉዓላዊነትና ልማት አስፈላጊ የሆነበትን ምክንያት እንዲሁም በሁለተኛው የዝግጅታችን ክፍል ደግሞ በናይጄሪያ ሴኪውሪቲስ እና ኤክስቼንጅ ኮሚሽን የሕግ እና ክስ ጉዳዮች መምሪያ ም/ዳይሬክተርና ኃላፊ ፍራንሲስ ኡዞማ ኦካፎር (ዶ/ር) ፣ በናይጄሪያ ሴኪውሪቲስ እና ኤክስቼንጅ ኮሚሽን የሕግ መምሪያ ዳይሬክተር ኔስተር ኢኬአጉ ፣ እንዲሁም በሴድረስ ግሩፕ አፍሪካ ሥራ አስፈፃሚ ዳይሬክተር ዴሌ አኪንጆን በአፍሪካ አህጉር ውስጥ የካፒታል ገበያ አስፈላጊነትን አስመልክቶ ያደረግነው ውይይት ተካትቷል፡፡  ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡

  50. 57

    የግብርና መድህን ሽፋን በኢትዮጵያ

    “የግብርና መድህን በአገራችን ውስጥ የሚፈለገውን ያህል አላደገም፡፡ ከአጠቃላይ ኢንዱስትሪው ከሚሰጠው የመድህን ሽፋን የግብርና ኢንሹራንስ ስናየው ከ 1 በመቶ አይዘልም፡፡ እስካሁን የተሰራው፡፡ እሱም ቢሆን ደግሞ በአብዛኛው ኮሜርሻል ፋርም ጋር የሚያያዝ ነው፡፡” ሲሉ የኢትዮጵያ የኢንሹራንስ ባለሙያዎች ማህበር ም/ፕሬዝደንት እንዲሁም የኢትዮጵያ ጠለፋ መድን አክሲዮን ማኅበር የስትራቴጂ እና ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፍቅሩ ፀጋዬ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ባለ ሁለት ክፍል ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል በኢትዮጵያ ውስጥ የግብርና መድህን ያለበትን ደረጃ እና አገልግሎቱን ተደራሽ በማድረግ ረገድ እያጋጠሙ ስላሉ የተለያዩ ተግዳሮቶች የኢትዮጵያ የኢንሹራንስ ባለሙያዎች ማህበር ም/ፕሬዝደንት እንዲሁም የኢትዮጵያ ጠለፋ መድን አክሲዮን ማኅበር የስትራቴጂ እና ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፍቅሩ ፀጋዬ ጋር የተወያየን ሲሆን፤ የሁለተኛውን የግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር ፕሮጀክት በይፋ የማስጀመር መርሀ-ግብር አስመልክቶ ያዘጋጀነው መሰናዶም ተካትቷል፡፡ ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

Type above to search every episode's transcript for a word or phrase. Matches are scoped to this podcast.

Searching…

No matches for "" in this podcast's transcripts.

Showing of matches

No topics indexed yet for this podcast.

Loading reviews...

ABOUT THIS SHOW

የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

HOSTED BY

ወሰንሰገድ አሰፋ

CATEGORIES

URL copied to clipboard!