EPISODE · Jul 9, 2026 · 1H
ከአሰላለፍ ነፃነት ወደ ስትራቴጂካዊ ሉዓላዊነት፦ የአፍሪካ አዲሱ የውጭ ፖሊሲ አካሄድ
from The Rising South
"አፍሪካውያን በዓለም አቀፍ ግንኙነት ውስጥ ሁለቱንም ወገን ተጠቃሚ የሚያደርግ አካሄድን ሲያስቡ፤ የትኛውንም ሀገር ውይም ቀጠና በፍፁም በዕውር ድንብር ማመን የለባቸውም። በመጀመሪያ ደረጃ አፍሪካውያን ማድረግ ያለባቸው ትልቁ ነገር በመካከላቸው እምነትን መገንባት ነው።" ሲሉ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር ዳዊት መዝገበ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ የአፍሪካ አገራት ጉብኝታቸውን ሐምሌ 30 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ጀምረው ነሐሴ 1 እና 2 2018 በኒጀርና ሞዛምቢክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉ ነው፡፡ ይህ በአህጉሪቱ ላይ ምን አዲስ የፖለቲካ አንድምታ ይዟል? ከቀዝቃዛው ጦርነት ዘመን የ"አሰላለፍ ነፃነት" (non-alignment) መርህ ወጥታ፣ አፍሪካ ዛሬ ወደምትከተለው ስትራቴጂካዊ ሉዓላዊነት እያደረገችው ያለው ሽግግር በተግባር ምን ማለት ነው? በዛሬው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅታችን፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር ከሆኑት ዳዊት መዝገበ (ዶ/ር) ጋር በመሆን፣ ተለዋዋጩን የአለም የኃይል ሚዛን እና የአፍሪካን አዲስ የዲፕሎማሲ በጥልቀት እንመረምራለን። ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ
Embed this episode
NOW PLAYING
ከአሰላለፍ ነፃነት ወደ ስትራቴጂካዊ ሉዓላዊነት፦ የአፍሪካ አዲሱ የውጭ ፖሊሲ አካሄድ
No transcript for this episode yet
Similar Episodes
No similar episodes found.
Similar Podcasts
No similar podcasts found.