EPISODE · Mar 10, 2026 · 1H
"ሩሲያ የዲሞክራሲያችን ጋሻ ናት" — ፕሬዝዳንት ፋውስቲን አርካንጅ ቱዋዴራ
from The Rising South
የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ፋውስቲን አርካንጅ ቱዋዴራ ከየካቲት 26 እስከ የካቲት 27 ፣ 2018 ዓ.ም በሩሲያ ሞስኮ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል። ከሩሲያ አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል። "የሉዓላዊነት መርሆዎችን እና የሰላም ጥረቶችን እንደግፋለን። የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ሕዝቧ አስቸጋሪ ጊዜያትን ያሳለፉ በመሆኑ፣ በዓለም ላይ ሰላም እንዲሰፍን ትፈልጋለች። ለዚያ ግብ ደግሞ መሥራት ይኖርብናል። ወደ ውይይት እና ድርድር ጠረጴዛ መቅረብ እና ከፍተኛ የሰው ሕይወት መጥፋትና የመሠረተ ልማት ውድመት እያስከተሉ ያሉ ጥቃቶችን በቀጥታ መፍታት አስፈላጊ መሆኑን እናምናለን።" ሲሉ የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ፋውስቲን አርካንጅ ቱዋዴራ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዛሬው የራይዚንግ ሳዉዝ ዝግጅታችን የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ፋውስቲን-አርቻንጅ ቱዋዴራ ስለ ቀጠናው ሰላም እና ስለ ሩሲያ ድጋፍ ከስፑትኒክ አፍሪካ ጋር ያደረጉት ልዩ ቆይታ፣ በእስራኤል፣ አሜሪካ እና ኢራን መካከል ስላለው ፍጥጫ የዓለም አቀፍ ጉዳዮች ተንታኙ ሞሃመድ ሲራጅ የሚሰጡት ሰፊ ማብራሪያ። የሀገርን ሉዓላዊነት ያስከበረው ታሪካዊው የካራማራ ድል ለኢትዮጵያ አንድነት ያለውን ፋይዳ የቆሮማሽ ማህበር ሰብሳቢ አቶ ደቻሳ አንገቻ ጋር ያደረግነው ውይይት ተካትተዋል። ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:
Embed this episode
Ready to play
"ሩሲያ የዲሞክራሲያችን ጋሻ ናት" — ፕሬዝዳንት ፋውስቲን አርካንጅ ቱዋዴራ
No transcript for this episode yet
Similar Episodes
No similar episodes found.
Similar Podcasts
No similar podcasts found.