EPISODE · May 14, 2026 · 1H
የአርሶ አደሮች የፈጠራ ክህሎት እና የሀገር በቀል እውቀት ሚና
from The Rising South
“እውቀት ፓስፖርት የለውም፤ እውቀት ተግባር (ልምድ) ነው ያለው። አርሶ አደሮቻችን ምርጥ ዘር ሲመርጡ 'ዝርያ ማሻሻል'፣ ዝናብን ሲተነብዩ ደግሞ 'የጥናት ዘዴ' እንበለው፤ ለሥራቸው ሳይንሳዊ ስሙን በመስጠት የሚገባቸውን ክብር ልንሰጣቸው ይገባል፡፡ ግባችን ጥገኝነት ሳይሆን ክብር፣ ጽናትና ሀገራዊ እራስን መቻል ነው፡፡” ሲሉ የመዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ 🔉በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ መሰናዶ፣ በመዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት "ከአርሶ አደሮች፣ ለአርሶ አደሮች፣ በአርሶ አደሮች" በሚል መሪ ቃል የተካሄደውን ልዩ አገር አቀፍ ጉባኤ እንቃኛለን። በጉባኤው ላይ አርሶ አደሮች እንደ ተመራማሪ ቀርበው ድንች በከርሰ ምድር የማቆየት ዘዴን እና የቴምር ምርትን በአካባቢያቸው የመመረት ስኬታማ የፈጠራ ስራዎቻቸውን አጋርተዋል።🗣በእንግድነት የመዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና እና የወሃ ልማት አስተዳደር እና ሃይድሮሎጂ ረ/ፕ እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው የዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክተር ዶ/ር ዓለማየሁ አባተ ተገኝተው፣ የአርሶ አደሩን ሀገር በቀል እውቀት ከዘመናዊ ምርምር ጋር በማቀናጀት ረገድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የፖሊሲ አውጪዎች ሚና ምን መሆን እንዳለበት ሰፊ ትንተና ይሰጡናል።
Embed this episode
NOW PLAYING
የአርሶ አደሮች የፈጠራ ክህሎት እና የሀገር በቀል እውቀት ሚና
No transcript for this episode yet
Similar Episodes
No similar episodes found.
Similar Podcasts
No similar podcasts found.