EPISODE · Nov 5, 2025 · 1H
የኢንቨስትመንት ባንክ ዘርፍ አጀማመር በኢትዮጵያ ፡ አዲሱ የፋይናንስ ምዕራፍ ጅማሮ
from The Rising South
“የሚሰራ የካፒታል ገበያ ካለህ፤ ገበያው በራሱ የረዥም ጊዜ ብድሮችንና ለዚያ የሚሆኑ ነገሮችን ያቀርባል፡፡ ባንኮች ደግሞ ለአጭር ጊዜ የሚሆኑ ዐይነት ብድሮችን ሊያቀርቡ ይችላሉ፡፡ ይህ በኢትዮጵያ ውስጥ የካፒታል ገበያ በምንፈልገው ደረጃ አለመኖሩን ተከትሎ የሆነ ነው፡፡ ሁሉም ነገር በተለመዱት ባንኮች በኩል እንደሚፈጸም ያሳያል፡፡ አንዳንድ ክፍተቶችም አሉ ፤ ሆኖም ክፍተቶቹ በካፒታል ገበያው የሚፈቱ ይሆናል፡፡” ሲሉ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ከፍተኛ አማካሪ አቶ ሲራክ ሰለሞን ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፤ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ከፍተኛ አማካሪ ከሆኑት አቶ ሲራክ ሰለሞን ጋር በመሆን ለውጥ ወዳልተለየው ወደ ኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ ዘልቀን በማደግ ላይ ያለውን የኢንቨስትመንት ባንክ ጅማሮን እንዳስሳለን፡፡ የካፒታል ገበያው መከፈትና የአዳዲስ የኢንቨስትመንትባንኮች ወደ ስራ መግባት ለባለሀብቶች፣ ለሥራ ፈጣሪዎች እና በአጠቃላይ ለሀገሪቱ ምጣኔ ሀብት ምን ይዞ ይመጣል? ምን አበርከቶ አለው? እድልና ፈተናዎቹስ ምንድናቸው? በሚሉ ጉዳዮች ላይ ቆይታ አድርገናል፡፡ ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡፡
Embed this episode
NOW PLAYING
የኢንቨስትመንት ባንክ ዘርፍ አጀማመር በኢትዮጵያ ፡ አዲሱ የፋይናንስ ምዕራፍ ጅማሮ
No transcript for this episode yet
Similar Episodes
No similar episodes found.
Similar Podcasts
No similar podcasts found.