EPISODE · Jun 4, 2025 · 1H
ያረጁ ትርክቶችን ልሳን መዝጋት: ደቡባዊ ዓለም መጪውን ጊዜ የሚቀረጽበት ሂደት
from The Rising South
በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት በደቡባዊው ትብብር ድርጅት /Organization of Southern Cooperation/ የቴክኖሎጂ ፈጠራ እና ዲጂታላይዜሽን ማበልጸግ ምክትል ዋና ጸኃፊ የሆኑት ሹመቴ ግዛው /ፒ.ኤች.ዲ/ የዓለም አቀፉ የኃይል ሚዛን ስለሚቀየርበት መንገድ ወሳኝ ነጥቦችን አጋርተዋል።“የደቡባዊው ትብብር ድርጅት በታላቁ ደቡባዊ ዓለም ውስጥ የሚገኙ ሀገራትን እና ማኅበረሰቦችን አቅም ማጎልበት ላይ ያምናል። ለአብነት ያህል ባህላዊ እና ሀገር-በቀል ዕውቀቶቻቸውን በመውሰድ ዓለም-አቀፍ በሆኑ መድረኮች ላይ እንዲሰሙ ያደርጋል።" በማለት ተናግረዋል።ምክትል ዋና ሥራ ፈጻሚዉ የዓለም-አቀፉ የፋይናንስ ሥርዓት ሀገራትን ዕዳ ውስጥ የሚዘፍቅ ነው በማለት ተችተዋል። የብሪክስን እሴቶች በሚጋራ መልኩ ባለብዙ ዋልታ እና ባለብዙ ዘርፍ የሆነ አዲስ ሞዴል እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል።የዓለምን ሥርዓት በመቀየር ሂደት ሚዲያ ወሳኝ ሚና ይጫወታል ሲሉ አስረድተዋል ፤ "ስፑትኒክ ሚዲይ እዚህ አፍሪካ-ኢትዮጵያ ውስጥ ቢሮውን በመክፈቱ እና ፍትህን፣ እኩልነትን፣ ሁሉን አካታችነትን እንዲሁም በራስ ፈጠራ ላይ መሠረትን ያደረገ ትርክት ሳይሆን መሬት ላይ ባለ ተጨባጭ እውነት ላይ ስለሚሠራ ያለኝን አድናቆት መግለጽ እፈልጋለሁ።" በማለት ገልጸዋል። የመጪውን ዓለም ሥርዓት የሚያስቃኘውን ይህንን የራይዚንግ ሳውዝ ፕሮግራም ይከታተላሉ።
Embed this episode
NOW PLAYING
ያረጁ ትርክቶችን ልሳን መዝጋት: ደቡባዊ ዓለም መጪውን ጊዜ የሚቀረጽበት ሂደት
No transcript for this episode yet
Similar Episodes
No similar episodes found.
Similar Podcasts
No similar podcasts found.