EPISODE · Nov 3, 2025 · 59 MIN
የሀገር-በቀል እውቀት፡ የማንነት እና የስነ-ልኬታችን መሣሪያ
from The Rising South
“የሀገር-በቀል እውቀት የስነ-ልኬታችን መሳሪያ ነው [……..] የአንድ ሰው፣ የአንድ ህዝብ፣ የአንድ ሃገር የጥሩ እና የመጥፎ ነገር መለኪያ ማለት ነው፡፡ ይሄ መጥፎ ነው፣ ይሄ ጥሩ ነው፣ ይሄ ይሻላል፣ ይሄ አይሻልም፣ ይሄ ይበልጣል ይሄ አይበልጥም ብሎ ህዝብ የሚበይንበት፣ የሚለካበት፣ ያሉትን እሴቶች የሚለካበት ነው፡፡ እሱ የለህም ማለት መለኪያህን ተነጠቅህ ማለት ነው፡፡ መለኪያህ ካንተ ወጣ ማለት በሌሎች መለኪያ ውስጥ ትገባለህ፡፡” ሲሉ በሀገር-በቀል እውቀት ጥናት እና ምርምር ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ አብዱልፈታህ አብደላህ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ የሀገር-በቀል እውቀት በመደበኛው የትምህርት-ሥርዓት ውስጥ የአለመካተቱን ምስጢር በሀገር-በቀል እውቀት ጥናት እና ምርምር ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ አብዱልፈታህ አብደላህ በሰፊው አብራርተውታል፡፡ በተጭማሪም በምስራቅ አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ ከፍተኛ የመነጋገሪያ ርዕሰ ጉዳይ እየሆነ ስለመጣው የቀይ ባህር ጉዳይ የታሪክ ተመራማሪ ከሆኑት ከፕሮፌሰር አህመድ ዘካሪያ ያደረነውም ውይይት በዚህ ዝግጅት ውስጥ ተካቷል፡፡ ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ :
Embed this episode
NOW PLAYING
የሀገር-በቀል እውቀት፡ የማንነት እና የስነ-ልኬታችን መሣሪያ
No transcript for this episode yet
Similar Episodes
No similar episodes found.
Similar Podcasts
No similar podcasts found.