EPISODE · Mar 15, 2026 · 10 MIN
የመጋቢት 06 ቀን 2018 የዓለም ዜና
from የዓለም ዜና · host DW
የኢትዮጵያ መንግሥት የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ የመሸጫ ዋጋ ላይ ያደረገውን ጭማሪ ተከትሎ በአዲስ አበባ የሕዝብ መጓጓዣ ከ5 እስከ 20 ብር የታሪፍ ማሻሻያ ተደረገ። የሩሲያ ጦር በዩክሬን በመካሔድ ላይ ለሚገኘው ጦርነት ኬንያውያንን በግዳጅ ከመመልመል እንዲታቀብ ግፊት ለማድረግ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሳሊያ ሙዳቫዲ ወደ ሞስኮ አቀኑ። በኮንጎ ሪፐብሊክ ዜጎች ድምጽ ሲሰጡ ዋሉ። አሜሪካና እስራኤል ከኢራን የገጠሙትን ጦርነት የቀሰቀሱ መሪዎች ውጊያውን እንዲያስቆሙ የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን ርዕሰ-ሊቃነ ጳጳሳት ሊዎ 14ኛ ጥሪ አቀረቡ። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በባርሴሎና እና በሴዑል የተካሔዱ የማራቶን የሩጫ ውድድሮችን አሸነፉ።
Embed this episode
NOW PLAYING
የመጋቢት 06 ቀን 2018 የዓለም ዜና
No transcript for this episode yet
Similar Episodes
No similar episodes found.