EPISODE · Dec 23, 2025 · 1H
የሩሲያ - አፍሪካ ግንኙነት ፦ አዳዲስ አድማሶች፣ ነባር ወዳጆች
from The Rising South
"በበርካታ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ሰላም በመጥፋቱ እንጨነቃለን፤ ምክንያቱም በአፍሪካ አህጉር ስለ ብልጽግና ማውራት የምንችለው ሰላም ሲኖር ብቻ ነው ብለን እናምናለን። ሰላም ካለ 'የምንመኛት አፍሪካ' ወደተሰኘው የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ-2063 ግቦች ለመድረስ መስራት እንችላለን። እንደ ሩሲያ ያሉ ሀገራት ለዓመታት ያካበቱትን ልምድና አቅም በመጠቀም የተሻለች ዓለምን መገንባት እንደምንችል እናምናለን።" ሲሉ የቦትስዋና የዓለም አቀፍ ግኑኝነት ሚኒስትር ፌንዮ ቡታሌ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል የቦትስዋና የዓለም አቀፍ ግኑኝነት ሚኒስትር የሆኑት ፌንዮ ቡታሌ (ዶ/ር) እና አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በካይሮ የተካሄደውን ሁለተኛው የሩሲያ-አፍሪካ የሚኒስትሮች ኮንፈረንስ አስመልክቶ ስለ ትብብር፣ የእጅአዙር ቅኝ ግዛት ፣ ስለ ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) እና ተያያዥ ጉዳዮች ሃሳባቸውን አጋርተውናል፤ በዝግጅታችን ሁለተኛው ክፍልም “የዓመቱ ማጠቃለያ ከቭላድሚር ፑቲን ጋር” የተሰኘውን ዓመታዊ ፕሮግራምን መሰረት በማድረግ በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ የውጭ ፖሊሲ እና ዲፕሎማሲ መምህር እና ተመራማሪ አበራ ሄጲሶ ጋር በመሆን በፕሮግራሙ ስለተነሱት አንኳር ነጥቦች ውይይት አድረገናል፡፡ ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ
Embed this episode
NOW PLAYING
የሩሲያ - አፍሪካ ግንኙነት ፦ አዳዲስ አድማሶች፣ ነባር ወዳጆች
No transcript for this episode yet
Similar Episodes
No similar episodes found.
Similar Podcasts
No similar podcasts found.