EPISODE · Jun 23, 2026 · 1H
የሰብአዊ እርዳታ ሉዓላዊነት፡- የሀገርን ነፃነትና ክብር የማስጠበቅ ተግባር
from The Rising South
"የሰብአዊ እርዳታ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ አሁን ላይ ለማንኛውም ሀገር ምርጫ አይደለም፤ በተለይም ስለ ሀገር ክብር፣ ነፃነት እና ሉዓላዊነት ለሚያስብ ሀገር ይህ ጉዳይ የግድ የሚል ተግባር ነው።" ሲሉ የብሄራዊ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዚህኛው ባለ ሶስት ክፍል የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፤ በመጀመሪያው ክፍል በአርኪኦሎጂ እና በሰው ልጅ አመጣጥ ላይ ያተኮረ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን የፓሊዮአንትሮፖሎጂ ተመራማሪዎች ከሆኑት ከዶ/ር በርሄ አስፋው እና ከዶ/ር ዮናስ በቀለ ጋር በመካከለኛው አዋሽ ስለተገኙ አዳዲስ የሳይንስ ግኝቶች እንወያያለን።በሁለተኛው ክፍል፤ የአፍሪካን የሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ አደጋዎች የመከላከል አቅም እንዲሁም ከውጭ እርዳታ ጥገኝነት የመውጣት አስፈላጊነትን በተመለከተ ከብሄራዊ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም ጋር የነበረንን ቆይታ እናቀርባለን።በመጨረሻም አፍሪካ ያላትን የተፈጥሮ ሀብት ተጠቅማ የምግብ ዋስትናዋን እንዴት ማረጋገጥ ትችላለች? በሚሉ ነጥቦች ዙሪያ ከአፍሪካ ህብረት የግብርና እና ምግብ ዋስትና ክፍል ተጠባባቂ ሃላፊ ዶ/ር ጃኔት ኤደሜ እና ከAGRA የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ዶ/ር ይሄነው ዘውዴ ጋር ያደረግነውን ውይይት አካትተናል።
Embed this episode
NOW PLAYING
የሰብአዊ እርዳታ ሉዓላዊነት፡- የሀገርን ነፃነትና ክብር የማስጠበቅ ተግባር
No transcript for this episode yet
Similar Episodes
No similar episodes found.
Similar Podcasts
No similar podcasts found.