PODCAST · news
ዜና መጽሔት
by DW
በዐበይት የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓ እና የዓለም ጉዳዮች ላይ ዜናዎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና ጥልቅ ትንታኔዎች ይቀርባሉ። በዐበይት የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓ እና የዓለም ጉዳዮች ላይ ዜናዎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና ጥልቅ ትንታኔዎች ይቀርባሉ። ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙ የዶይቼ ቬለ ዘጋቢዎች የሚያጠናቅሩት ዜና መፅሔት ከሰኞ እስከ አርብ ከዓለም ዜና ቀጥሎ ይቀርባል። የዶይቼ ቬለን ሥርጭት በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በቀጥታ ማድመጥ ይቻላል። በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ የዶይቼ ቬለን ዜና መጽሔቶች ያዳምጡ።
-
100
የግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
መተከል ዞን ጉባ ወረዳ ከ30 በላይ መንገደኞች በታጣቂዎች መገደላቸዉን የሚያወሳዉን ዘገባ ያስቀድማል።የህወሓት አባላት ናቸዉ የተባሉ ታጣቂዎች ከራያ አለማጣ ከተማ 50 የቤተ-ክሕነት ተማሪዎች ማገታቸዉ ከደሴ ሲዘገብ፣ የኢትዮጵያ የሲቪል ማሕበራት ሕብረት አንዳድ አካባቢ በመራጮች ምዝገባ ሒደት ሕግ መጣሱን አስታዉቋል።ዜና መፅሔቱ የትግራይ ጋዜጠኞች ከክልሉ ወደ ሌላ አካባቢ ለመሔድ መገደዳቸዉን የሚቃኝ ዘገባም አለዉ።
-
99
የግንቦት 4 ቀን 2018 የዜና መፅሔት
የዓለም ዜናውን በሚከተለው የዜና መጽሔት፣-በዋግ ኸምራ ዞን የአበርገሌ ወረዳ ተፈናቃዮች አቤቱታ፤ ዓለም አቀፉ የፍልሰኞች ድርጅት የአፍሪካ ቀንድ ፍልሰተኞች በአደገኛው መስመር መጓዛቸውን አላቆሙም ማለቱ፤ የኢትዮጵያ የምርጫ ስርዓት፤ አብላጫ ድምጽ ወይስ ተመጣጣኝ? ፤ የአውሮፓ ሕብረት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የስብሰባ ትኩረት እንዲሁም ከመሬት ለአራሹ ትግል እስከ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የዘለቁትና ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት አቶ ዘገየ አስፋውንም የሚያስታውስ ጥንቅር አካቷል።
-
98
የግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
በዜና መፅሄት ጥንቅራችን -ለሰባተኛው ዙር ምርጫ የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በገንዘብ ድልድል ላይ ያቀረቡት ቅሬታ -የኢኮኖሚ ዕድገት መመዘኛ የሕዝቡን የኑሮ ሁኔታም ከግምት ማስገባት አለበት መባሉን -የአየር ንብረትን መቋቋም የሚያስችል የግብርና ቴክኖሎጂን የተመለከተ ዓለም አቀፍ ስብሰባ በሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ መካሄዱን -የኢራን የሰላም ዕቅድ በአሜሪካ ውድቅ መሆኑን የተመለከቱ ዘገባዎች ተካተዋል።
-
97
የዓርብ ሚያዝያ 30 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ዜና መጽሔት
ቀዳሚውን የዓለም ዜና በሚከተለው የዜና መጽሔት -የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)የቅድመ ምርጫ ሂደቶች ላይ ጥሰቶች እንደነበሩ መግለጹ ፣በአማራ ክልል በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚሳተፉ ተፎካካሪ ሀገራዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች ስሞታ፣ ስለ መገናኛ ብዙኃን ምኅዳር የመንግሥት፣ የባለሙያዎች እና አጥኚዎች ዕዉነት፣ -የነዋሪዎችን ህይወት ያቃወሰው የትራንስፖርት እጥረት በኢትዮጵያ፣ -የሞት ፍርድን የሚጠባበቁትን ጨምሮ ሰነድ አልባዎቹ ኢትዮጵያዉያን በሳዉዲ፣ የዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን ተኩስ አቁም ወዴት ያመራ ይኾን? በተሰኙ ርዕሶች ስር የተጠናቀሩ ዘገባዎች ይቀርባሉ ሳምንታዊ የወጣቶች ዓለምም በሰዓቱ ይቀርባል።
-
96
የሚያዚያ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
በዜና መጽሔት የደቡብ አፍሪቃው ዘመቻ ዱዱላ’ ኢትዮጵያዉያንን ጨምሮ ሕገ-ወጥ ስደተኞችን እያደነ ነው፤ የወለንጪቲ የልማት ተነሺ ገበሬዎች ካሳ አልተከፈለንም ሲሉ ማማረራቸውን፤ የሙዝ አምራች አርሶ አደሮች የገበያ ተግዳሮት ፤ ዩናይትድ ስቴትስ ለኢትዮጵያ የምትሰጠው ርዳታ እንዳይቋረጥ መጠየቁ እንዲሆም ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ከምትልካቸው ምርቶች 10 ቢልዮን ዶላር ለማግኘት ማቀዷ በሚሉ ርዕሶች ስር የተቀናበሩ ዘገባዎች ይቀርባሉ።
-
95
የሚያዚያ 28 ቀን 2018 ዓ/ም የዜና መጽሔት
አሜሪካ የኤርትራን ማዕቀብ ለማንሳት ማጤኗ ለኢትዮጵያ በረከት ወይስ መዘዝ? ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ ኢትዮጵያውያን በተለየ መንገድ የጥቃት ኢላማ መሆናቸው የአላማጣና አካባቢው ወጣቶች የጦርነት ሥጋትና ስደት የሱዳን ክስና እና የኢትዮጵያ ምላሽ ህወሓት ትናንት የወሰደው 'ርምጃ እና የሚኖረው ውጤት
-
94
የማክሰኞ ሚያዝያ 27 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ዜና መጽሔት
ዛሬ ታስቦ የዋለዉን 85ኛ የኢትዮጵያዉያን የድል በዓል መታስብያን በማስታከክ ፤ የአርበኞች ድል መታሰቢያ እና የዛሬው ትውልድ ለሕብረት ያለው አቋም ሲል የሚያጠይቅ ዘገባን ይዘናል። ለ7ኛዉ ጠቅላላ ምርጫ ቅስቀሳ ተግዳሮት ገጠመን ያሉ ተፎካካሪ ፓርቲዎች በደቡብ ወሎ ዞን እንዲሁም በኢትዮጵያ የነዳጅ ዋጋ ላይ የተደረገው የመሸጫ ዋጋ ጭማሪ እና የሚያሳድረዉ ጫናን የሚዳስስ ዘገቦችም በተከታታይ ይቀርባሉ። የአሜሪካዉ ትራምፕ በጀርመን ከሰፈሩ የአሜሪካን ወታደሮች መካከል ወደ 5,000 የሚሆኑትን ለማስወጣት እቅድ መያዛቸዉ እና የተሰጡ ግብረ መልሶችን የሚዳስስ ዘገባንም ይዘናል።
-
93
-
92
የሚያዝያ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
የደቡብ አፍሪቃው መጤ ጠል እንቅስቃሴ ኢትዮጵያውያንን ብርቱ ስጋት ላይ ጥሏል አውሮፓ ሕብረት የፕሪቶሪያን ስምምነት አደጋ ላይ የሚጥሉ 'ርምጃዎች እንዲረግቡ ጠየቀ “አገልግሎታችንን ወደ አምስት ኮከብ ማሳደግ እንፈልጋለን” የኢትዮጵያ አየርመንገድ ዓለም አቀፉ የሠራተኞች ቀን በኢትዮጵያ ሲታወስ ወደ ከተሞች የሚደረግ ከፍተኛ ፍልሰት የቤት አቅርቦት ቀውስ ፈጥሯል-ተመድ
-
91
-
90
የሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
ለኦሮሚያ ክልል ዘላቂ ሰላም መፍትሄ የሚሻው የወጣቶች ምክክር ፣ በአማራ ክልል የነዳጅ እጥረት ያስከተለው የኑሮ ምስቅልቅል ፣ ኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር የጀመረው የብትን ጭነት አገልግሎት ለኢትዮጵያ ይዞ የመጣው ዕድል ፣ «በኢትዮጵያ አካታች ዕርቅ ይምጣ» የኢትዮጵያውያን ሕዝባዊ ማኅበራት ጉባዔ በአሜሪካ፣ እንዲሁም አፍሪቃ ወደ ኋላ የቀረችበት የተመድ የምዕተ ዓመቱ የልማት ግቦች የትኞቹ ናቸው
-
89
የሚያዝያ 20 ቀን 2018 የዜና መፅሔት
በዜና መጽኄት አምስት ዘገባዎችን እናስተነትናለን ።የኢትዮጵዊያን ግድያ በጆሃንስበርግ ፤ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች እና ምርጫ ፤ ቁልፍ መሠረተ ልማቶችን ለመጠበቅ የተረቀቀው የሳይበር ደህንነት አዋጅ ምን ይዟል? እንዲሁም የትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ወቅታዊ መግለጫ ይሰኛሉ ዘገባዎቹ ።
-
88
የሚያዝያ 19 ቀን 2018 ዓ.ም የዜና መፅሔት
በዜና መጽሔት፤ የመረጃ ነጻነት ረቂቅ አዋጅ መብት እንዳይገድብ መጠየቁ ፤ ምርጫ ቦርድ የጸጥታ ሁኔታዎችን የሚያጣራ ቡድን ማሰማራቱ፤ ከፀሐይ ኃይል የሚያመነጭ ቴክኒዎሎጂ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ እንዲሁም የአፍሪካ የፖሊሲ አውጭዎች ለሰው ሠራሽ አስተውሎት ትኩረት እንዲሰጡ የዘርፉ ባለሙያ ማሳሰባቸውን የሚያስቃኙ ዘገባዎች አካቷል።
-
87
የሚያዝያ 16 ቀን 2018 ዓ.ም የዜና መፅሔት
በዜና መጽሔት፤ በአርሲ ዞን ሮቤ ዲዳዓ ወረዳ ንጹሐን ላይ የተፈጸመው ጥቃት፤የአፍሪካ ሃገራት በሰብዓዊ መብት ላይ የሚተላለፉ ውሳኔዎችን እንደማይተገብሩ ተገለፀ በ614 ምርጫ ክልሎች ላይ ምርጫ እንደሚያካሂድ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መግለጹ፤ ተዛብተው ተጽፈዋል የተባሉ ታሪኮች እንዲታረሙ ያሳሰበው የኦሮሞ ምርምር ማሕበር ጉባኤ ፤እንዲሁም እስራኤል እና ሊባኖስ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ለሦስት ሳምንት መራዘሙን የሚያስቃኙ ዘገባዎች አካቷል።
-
86
የሚያዝያ 15 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
የይገባኛል ጥያቄ በሚነሳባቸው እና አወዛጋቢ በሆኑት የምዕራብ ትግራይ አካባቢዎች የመብት ጥሰት እየተፈፀመ ነው ሲል ሂውማን ራይትስ ወች መግለፁን ኢትዮጵያ ከነዳጅ ወደ ኤለክትሪክ መኪኖች ሽግግር እያደረገች መሆኑን፤ በኢትዮጵያ እያደገ የመጣውን የኤለክትሪክ መኪና አጠቃቀም፣ እና መቋጫ ባጣው የአሜሪካ እና የኢራን ውዝግብ እንዲሁም የተዘጋው ሆርሙዝ ወሽመጥ
-
85
የሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ዜና መፅሄት
የዜና መጽሔታችን በአበርገሌ ወረዳ ስለተከሰተው ግጭት፤ የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመወዳደር ያቀረበውን ጥያቄ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሳይቀበለው መቅረቱ፤ የአውሮፓ ኮሚሽን ለአፍሪካ አገራት የበሽታ መከላከልና መቆጣጠሪያ ፕሮጀክት የሚውል ዕርዳታ መስጠቱ፤ እንዲሁም የአውሮፓ ኮሚሽን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ያስተላለፉት ውሳኔና አንደምታ በተመለከተ ከብራስልሱ ወኪላችን ያደረግነው አጭር ቆይታ ይዳሰሳሉ።
-
84
የሚያዚያ 13 ቀን 2018 ዓ.ም የዜና መፅሄት
b,ዛሬ የዜና መጽሔታችን ለብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ሰፊ ሥልጣን የሰጠው "የአቪዬሽን ደኅንነት" ማሻሻያ አዋጅ መፅደቅ፣ የነዳጅ እጥረት እና የትራንስፖርት ዋጋ መጨመር በአሶሳ ፣’"ከፍተኛ የገንዘብ ቅጣት እየተጣለብን ነው" ሲሉ የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች መግለፃቸው ፣እንዲሁም ቀነ ገደቡ እየተጠናቀቀ ያለው የተኩስ አቁም እና ተጠባቂው የኢስላማባድ ድርድር በተሰኙ ዘገባዎችን አካቷል። በቅደም ተከተል ይተነተናሉ።
-
83
DW Amharic የሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዜና መጽሔት
ህወሓት ከ2013 ዓ.ም በፊት የነበረው የትግራይ ክልል ምክር ቤት ወደ ሥራ እንዲመለስ ወሰነ፣ ሕገወጥነትን ሕግ እንዴት ይቆጣጠረው? ጋዜጠኛ ሚሊዮን በየነ «አሁንም ያለበት ቦታ አይታወቅም» - አዲስ ስታንዳርድ
-
82
የሚያዝያ 9 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ዜና መጽሔት
በዓለም ዜና የሚጀምረዉ የአንድ ሰዓቱ ስርጭታችን፤ በዜና መጽሔት ጥንቅሩ፤ 1, የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ እና መልስ የማግኛዉ መንገድ 2, በአማራ ክልል መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ተፈናቃዮች ወደ ቀያችን እንመለስ ጥሪ 3, ሕገ ወጥነትን ሕግ እንዴት ይቆጣጠረው? 4, በግጭት አፈታት እና በሰላም ግንባታ ላይ የተካሄደ ጉባኤ እንዲሁም 5, ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊነት የሚወዳደር የጋራ ዕጩ ያላፀደቀችዉ አፍሪቃ የተሰኙ ርዕሶችን አካቷል።
-
81
የዜና መጽሔት፤ ሚያዝያ 8 ቀን 2018 ሐሙስ
በአማራ ክልል ራያ ቆቦ ወረዳ በጸበል ቦታ በደረሰ ድንገተኛ የጎርፍ አደጋ 8 ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። በአደጋው ከ30 በላይ ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም። የአዲስ ስታንዳርድ የበይነ መረብ መገናኛ ብዙኃን ማኔጂንግ ኤዲተር ትላንት ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ከሥራ ገበታው ከተወሰደ በኋላ ዛሬም የደረሰበት አልታወቀም። ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ ሁለት የፖሊስ መኮንኖች እና አንድ የመከላከያ ሠራዊት አባል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በታጣቂዎች ተገድለዋል። በዛሬው ዜና መጽሔት ከሚቀርቡ ዘገባዎች መካከል እነዚህ ይገኙበታል።
-
80
የሚያዝያ 7 ቀን 2018 የዜና ፅሔት
በዜና መጽኄት አራት ዘገባዎችን እናስተነትናለን ። ኢሕአፓ የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ በሚመለከት ለምርጫ ቦርድ ደብዳቤ መጻፉን ገለፀ፤ ደቡብ ወሎ ዞን ፓስፖርት ለማውጣት 161 ሐሰተኛ ሰነዶች፤ የኢራኑ ጦርነት፣ ለሱዳኑ ግጭት የሚሰጠው ትኩረት እንዲቀንስ ማድረጉ ተገለፀ እንዲሁም የዩናይትድ ስቴትስ የመርከቦች እገዳ በፍኖተ ሆርሙዝ ለኢራን ምን አመጣ? ይሰኛሉ ዘገባዎቹ፣
-
79
የሚያዚያ 6 ቀን 2018፤ የዜና መፅሄት
ዜናውን ተከትሎ በሚቀርበው የዛሬ የዜና መፅሔታችን ፤መራጮች ምን ይላሉ?፣በነጻ የንግድ ቀጠና ባለሃብቶችን ከገቢ ግብር ነጻ የሚያደርገው መመሪያ፣በአማራ ክል ተፈናቃዮች የምግብ ዕርዳታ ከተሰጠን 2 ወራት አለፉ ማለታቸውን ፣እንዲሁም የመካከለኛው ምስራቅ ወቅታዊ ሁኔታ የሚዳስሱ ጥንቅሮች አካቷል። ሳምንታዊዎቹ ጤና እና አካባቢ እና አውሮፓ እና ጀርመን ዝግጅቶችም ተካተዋል።
-
78
የመጋቢት 5 ቀን 2018 የዜና መፅሔት
ዜና መጽሔት ጥንቅሩ፤ የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት እና በሂደት የሚያስከትለው ጫና፤2, በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኮንሶ ዞን ነዋሪዎችን እየፈተነ ያለዉ የኤሌክትሪክ መቋረጥ፤ በተለያዩ የዓማር ክልል ከተሞች የንግድ ማህበረሰቡን የሚያጭበረብሩ ግለሰቦች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ እንዲሁም ባለፈዉ ሰሞን በባሌ ሮቤ መናኸሪያ ላይ በወጣት ወንጀለኞች ተደበደቡት አባት የተሰኙ ርዕሶችን አካቷል።
-
77
DW Amharic የሚያዝያ 02 ቀን 2018 ዜና መጽሔት
የነዳጅ እጥረት፣ የመጓጓዣ ዋጋ እና የጤፍ አቅርቦት፤ የመሠረታዊ የፍጆታ ምርቶች ዋጋ መጨመር፤ ኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ ሕብረት የሠላምና ፀጥታ ምክር ቤት የአንድ ወር ሊቀመንበር ሆነች፤ የእስራኤል-ዩናይትድ ስቴትስና የኢራን ተኩስ አቁም ያሳደረዉ ተስፋ በኢትዮጵያ፤ የአሜሪካና ኢራን ጦርነት የተኩስ አቁም ስምምነት
-
76
-
75
የመጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ ም ዜና መጽሔት
የዜና መፅሔት ዝግጅታችን፣የትግራይ ክልል ጊዚያዊ ፕሬዝደንት የጄኔራል ታደሰ ወረደ ዘመነ-ሥልጣን ለተጨማሪ አንድ ዓመት መራዘሙንና ያስከተለዉን ቅሬታ የሚቃኘዉን ዘገባ ያስቀድማል።በአማራ ክልል ዋግኽምራ ዞንን የመታዉ ድርቅ ከሁለት ወረዳ ብቻ ከ4000 በላይ ሰዎች መፈናቀላቸዉ ተሰምቷል።የአፍሪቃ ሕብረትና የኢትዮጵያ መሪዎች በአንጋፋዋ ኢትዮጵያዊት ዲፕሎማት ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ሞት የተሰማቸዉን ሐዘን እየገለፁ ነዉ። ዜና መፅሔቱ ዩናይትድ ስቴትስ፣ እስራኤልና ኢራን ለሁለት ሳምንት ተኩስ ማቆማቸዉን፣ ምክንያቱንና የወደፊቱን ሁኔታ በተመለከተ ከባልደረቦቻችን ጋር የቀጥታ ዉይይት ይሰማበታልም።
-
74
የመጋቢት 29 ቀን 2018 የዜና መጽሔት
በዜና መጽኄት አራት ዘገባዎችን እናስተነትናለን ። ዘገባዎቹ፦ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው የመረጃ ነጻነት ረቂቅ አዋጅ ምን ይዟል?፤ በነዳጅ እጥረቱ የተስተጓጎለው ትራንስፖርትና መጪው የበዓል ሸመታ፤ የነዳጅ እጥረት በአማራ ክልል የፍትህ ስርዓት ላይ እንቅፋት እየሆነ ነው መባሉ ይሰኛሉ ። እንዲሁም የዪናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ለኢራን የሰጡት ቀነ ገደብ ሊጠናቀቅ ጫፍ መድረሱ እና ያጠላው ሥጋት የሚዳስስ ቃለ መጠይቅ ይኖረናል
-
73
የመጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
በዜና መጽሔት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ የመራጮች ምዝገባን ማራዘሙ በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ያለው ጦርነት በማዳበሪያ አቅርቦት ላይ የፈጥረው ተፅዕኖ የለም መባሉ በአረብ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እሳት እየለበለባቸው የሚያገኙትን ገንዘብ እንዲያጠራቅሙላቸው ወደ አገር ቤት ሲልኩ መከዳታቸው የአሜሪካው ፕረዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን የሆርሙዝ የባሕር በር ለመክፈት ስምምነት ላይ እንድትደርስ የሰጡት ቀነ ገደብ ነገ ያልቃል በዚህና ተያያዥ ጉዳዮች ከዋሽንግተን ዲሲ ወኪላችን አጭር ቆይታ ይኖረናል።
-
72
የመጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ፤የዜና መፅሄት
በዛሬው የዜና መፅሔታችን በጅቡቲ መኪኖቻቸው ያለስራ የቆሙባቸው የነዳጅ ጫኝ ቦቴ አሽከርካሪዎች ምሬት፤የአሜሪካ መንግስት በኢትዮጵያ ላይ ያወጣው የጉዞ ማስጠንቀቂያ፤ኢትዮጵያ አሳካሁ ያለችው የ13 ቢሊየን ዶላር ኢንቨስትመንት አንድምታ፤እንዲሁም አዲሱ የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ የሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ተካተዋል።
-
71
የመጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
የስደተኞች ሰቆቃ በየመን እና በሳውዲ አረቢያ ድንበር ላይ በትግራይ ክልል እና ውዝግብ ባለባቸው ቦታዎች የመራጮች ምዝገባ ምን ይመስላል? ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ኢትዮጵያን መምራት የጀመሩበት ስምንተኛ ዓመት የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት የአፍሪካ አገራትን ገንዘብ ማዳከም ጀምሯል ዶናልድ ትራምፕ ስለ ኢራን ጦርነት ለህዝባቸው ያስተላለፉት መልዕክት
-
70
የመጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
በዜና መጽሔት ዝግጅታችን አዲስ አበባ ውስጥ የተሰየመው የትግራይ ምክክር እና አንድምታው፤ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አዲሱ “የህገወጥ ቤቶች ግንባታ” ደንብ እና ያስተናገደው አስተያየት ፤ገቢና ወጪ ሸቀጦችን የሚያጓጉዙ ከባድ ተሽከርካሪዎች በነዳጅ እጥረት ሥራቸው በምን ኹኔታ ላይ ይገኛል? የሚለውን ጨምሮ ፤ በነዳጅ እጥረት ቀውስ በሃዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ላይ ያሳደረው ተጽዕኖን የተመለከቱ ዘገባዎች በዝርዝር የሚቀርቡ ርዕሰ ጉዳዮቻችን ናቸው ።
-
69
DW Amharic የመጋቢት 22 ቀን 2018 የዜና መጽሔት
የኢራኑ ጦርነት የኢትዮ-ኤርትራን ውጥረት ያባብሰዋል ብለው እንደማያምኑ ተንታኞች ተናገሩ፤ እስካሁን የተቋረጠ የአገር ውስጥም ሆነ ዓለማቀፍ በረራ አለመኖሩንም ስራ አስፈጻሚው ገልጸዋል፡፡ የቅድስት ክፍሌ መታሰቢያ የመንገድ ደሕንነት ትምሕርት፤ የነዳጅ ዕጥረት እያስከተለው ያለው ጫና፤ የኢራን ጦርነት በአውሮፓ ሐገራት ያሳደረው ጫና
-
68
የመጋቢት 21 ቀን 2018 የዜና መፅሔት
የዜና መጽሔት አራት ርዕሰ ጉዳዮች ይተነተናሉ እነርሱም በኦሮሚያ ክልል የተኩስ ድምጽ እንዲቆም የቀረበው ጥሪ ፣ በደቡብ ራዲዮ እና ቴሌቪዥን ድርጅት የወልቂጤ ቅርንጫፍ FM 89.2 ሠራተኞች የስራ ማቆም አድማ ፣ በትግራይ ክልል ሀገራዊ ኹነቶችን ለማከናወን ያለው ወቅታዊ ኹኔታ እንዲሁም የሁቲዎች ጥቃትና ማስጠንቀቂያ በአፍሪካ ቀንድ ስጋት እንዲጨምር ማድረጉ የሚሉት ናቸው። ማኅደረ ዜና ለዛሬ ትኩረቱን የመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ በኢትዮጵያ ያስከተለውን ችግር ላይ አድርጓል።
-
67
የመጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
በዜና መጽሔት የኢትዮጵያ ሀገራዊ የውይይት ኮሚሽን የትግራይ ክልልልን አጀንዳ ልየታ በአዲስ አበባ፤ የነዳጅ እጥረት በአዲስ አበባ እያስከተለ ያለውን ችግር የጋምቤላ ክልላዊ መንግስት ከ300 በላይ የፖሊስ መኮንኖችን ከስራ ማባረሩን እንዲሁም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአፍሪቃ የባሪያ ንግድ ላይ ያሳለፈውን ውሳኔ መቀበላቸው የሚቃኙ አራት ዘገባዎች ይቀርባሉ።
-
66
-
65
የረቡዕ መጋቢት 16 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ዜና መጽሔት
የዓለም ዜናን ተከትሎ፤ "ከምርጭ ራሳችንን እስከማግለል ርምጃ ልንወስድ እንችላለን" ሲል የ4 ፓርቲዎች ጥንር የሆነው ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ መግለፁን፤ስለምርጫው የታጣቂዎች ማስጠንቀቂያ እና የፓርቲዎች አቋም የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን በዛሬው ዕለት አዲስ የአፍሪካ ቀንድ እና የቀይ ባሕር ልዩ መልዕክተኛ መሾሙን እንዲሁም የአሜሪካ እና የኢራን የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴን የሚቃኙ አራት ዘገባዎች ይኖሩናል።
-
64
የመጋቢት 15 ቀን 2018 ዓ.ም የዜና መፅሔት
ዜና መጽሔት ጥንቅራችን አራት ዘገባዎች ይኖሩናል። እነሱም፤* በሱዳኗ ኩርሙክ የተከሰተው ግጭት የድንበር ነዋሪዎች ላይ የፈጠረው ስጋት፤* የሶማሌ ክልል የክልሉን ከፍተኛ ባለስልጣናትን ስም በሀሰተኛ መረጃ ለማጠልሸት እየተካሄደ ነው ያለውን ድርጊት መኮነኑ፤* የትግራይ ቴሌቪዥን ጋዜጠኛ ዮሐንስ ብርሃነ በአስቸኳይ እንዲፈታ ስለ መጠየቁ እና* በሰሜን ሸዋ ዞን ሰላሌ፤ በጠለፋ ምክንያት ለአስከፊ ጉዳት የተዳረገች የ7ኛ ክፍል ተማሪ ጉዳይ ናቸው።
-
63
የመጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ/ም የዜና መጽሔት
-በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ኬንያ ለመሻገር ሙከራ ማድረጋቸው የተገለፀ 48 ኤርትራውያንን ማሰሩን የደቡብ ኦሞ ዞን ፖሊስ አስታውቋል። -ጂግጂጋ ውስጥ በደረሰ የእሳት አደጋ ከ40 በላይ ሱቆች መቃጠላቸውን የሶማሌ ክልል አስታወቀ እነዚህና -በዋግ ህምራ ዞን በእደ ጥበብ ባለሙያዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እንዲሁም አዲሱ የዩናይትድ ስቴትስ የቪዛ አሰጣጥ ሕግ
-
62
የመጋቢት 11 ቀን 2018 የዜና መፅሔት
የዛሬው የዜና መፅሔታችን በዒድ በዓል ላይ ያተኮረ ነው። በአዲስ አበባ፣ በኦሮሚያ፣በድሬዳዋ፣በሐዋሳ እና በደሴ የነበረው የበዓሉ ድባብ ያስቃኘናል።
-
61
የሐሙስ መጋቢት 10 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ዜና መጽሔት
የዜና መጽሔት -በኢትዮጵያ ወቅታዊ ዲፕሎማሲ ላይ የሚሰጡ አስተያየቶች ፣ -በትግራይ ክልል "አፈና እና የዘፈቀደ እሥራት" መኖሩን አንድ የሲቪክ ድርጅት መግለጹ አማርኛ ለምን ከአፍሪካ ህብረት የሥራ ቋንቋዎች አንዱ ሳይሆን ለምን ቀረ? -የነዳጅ ዋጋ ንረት በአሶሳ ፣ እንዲሁም የተወደደው የዒድ ገበያ በደሴ በተሰኙ ርዕሶች ስር የተጠናቀሩ ዘገባዎች ተካተዋል። ሳምንታዊው የባህል መድረክ በኢትዮጵያ የብርሌ ታሪክ ላይ ያተኩራል ።
-
60
የመጋቢት 9 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
በዜና መጽሔት በአማራ ክልል የነዳጅ ዘይት እጥረት የፈጠረው የትራንስፖርት አገልግሎት መስተጓጎል፤ ባለፉት ሰባት ዐመታት በኦሮሚያ ክልል እየተካሄደ ያለው ግጭት እና ተፅዕኖው፤ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ለዶ/ር ሲሳይ አውግቸው ተፈቅዶ የነበረውን የዋስትና መብት መሻሩ ፤ እና የኢትዮጵያ ብር የመግዛት አቅም ቢያንስ በአንድ በመቶ ቅናሽ ማሳየቱን እንቃኛን
-
59
የመጋቢት 8 ቀን 2018 ዓ/ም የዜና መጽሔት
የተቃዋሚ ፓርቲዎች የምርጫ ዘመቻ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በኢትዮጵያ ሴቶች ላይ የተፈፀሙ በደሎችና የፍትሕ ጥያቄ፣ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ማሕበር በካናዳ፣ እና የአፍሪቃ ሐገራት አቋም በመካከለኛዉ ምሥራቅ ጦርነት
-
58
የመጋቢት 7 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ዜና መጽሔት
በዜና መጽሔት -በኢትዮጵያ የነዳጅ አጠቃቀም በቁጠባ እንዲሆን ማሳሰቢያ መሰጠቱ ፣ - በሰሜን ወሎ ዞን ሙጃ ወረዳ በውጊያ ምክንያት መንገዶች መዘጋታቸው በነዋሪዎች ላይ ያስከተለው ማኅበራዊ ቀውስ - የሆርሙዝን ወሽመጥ ለማስጠበቅ የአሜሪካን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ያቀረቡት የእርዳታ ጥሪና የአውሮጳ ኅብረት እንዲሁም የጀርመን የምርጫ ስርዓትና ጠቃሚ ልምዶች በተሰኙት ርዕሶች ስር የተቀናበሩ ዘገባዎች ይቀርባሉ።
-
57
-
56
የመጋቢት 3 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
በዜና መጽኄት የ«ፋይዳ» ዲጂታል መታወቂያ፡ በቴክኖሎጂ እድገት እና በዜጎች መብት መካከል ያለው ሚዛን፤ የጦርነት ስጋት ያዣበበባት ትግራይ ክልል እና የህወሓት አስገዳጅ የገንዘብ ማሰባሰብያ ፤ በአዲስ አበባ እና ደሴ መንገድ የአሽከርካሪዎችና ተጓዦች የደኅንነት ሥጋት ማየሉ፤ ነጻ ሚዲያ የሚኖረው ሚና ትኩረት እንዲሰጠው መጠየቁ፤ እንዲሁም የጀርመን የፌዴራሊዝም ሥርዓት አተገባበር እና ልዩ መገለጫው ይሰኛሉ ዘገባዎቹ ።
-
55
የመጋቢት 2 ቀን 2018 የዜና መፅሔት
የዓለም ዜናን በሚከተለው የዜና መጽሔት በኢትዮጵያ ህዝባዊ እምቢተኝነትን አሰመልክቶ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ፣ በጋሞ ዞን በናዳና ጎርፍ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ቢያንስ 64 መድረሱ፣ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪው እና የኑሮው ጫና እንዲሁም በፖላንዱ የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፕዮና የሚሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቶች ቡድን ያጋጠመው የቪዛ ችግርን ይዳስሳል።
-
54
-
53
የየካቲት 30 ቀን 2018 ዓም የዜና መጽሔት
--በጦርነት ግጭት ዉስጥ የሴቶች ከፍተኛ ተጋላጭነት እልባት ያሻዋል ሲል የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ (ኦፌኮ)መግለጫ ማዉጣቱ --የአፍሪካ ሕብረት የሴቶችን ውክልና የበለጠ እንዲያሳድግ መጠየቁ --የሲቪል ነዋሪዎች ደህንነት እንዲጠበቅ የጠየቀዉ ጎጎት ለጉራጌ አንድነትና ፍትህ ፓርቲ --በደላንታ ወረዳ የኦፓል ማዕድን አምራቾች በሰላም እጦት ምክንያት ስጋት ውስጥ ነን ማለታቸዉ እንዲሁም -መዲና በርሊን የሚገኘዉ የጀርመን የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር የኢትዮጵያ እና የጀርመንን ግንኙነት የተመለከተዉ ስብሰባ
-
52
የየካቲት 27 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ -ኢንተርናሽናል የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊትን ፣ሴቶችን በጅምላ የመድፈርና የማሰቃየት ወንጀሎችን ጨምሮ በበርካታ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መክሰሱ ፣ -ነገ ስለሚጀመረው የመራጮች ምዝገባ የተሰበሰቡ የህዝብ አስተያየቶች፣ -በኢትዮጵያ በኬንያና በሶማሊያ የሚገኙ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ለድርቅ መጋለጣቸው -ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም አትሌቲክስ የ"አንድ ቀን ውድድር" እንደምታዘጋጅ መገለጹ
-
51
የየካቲት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
የዛሬው የዜና መጽሔት ዝግጅታችን 41 ሐገሮች በኢትዮጵያ ያለውን የመናገር ነጻነትና የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳሳሰባቸው መግለጻቸውን፤ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሞሽን በአርሲ ስለተገደሉ ዜጎች ያወጣውን መግለጫ፤ ከራያ አላማጣ፣ ኮረምና ኦፍላ ዛታ የተፈናቀሉ ወገኖች የዕርዳታ ጥሪ፤ በምዕራባዊ የሐገሪቱ ክፍል ከመደበኛ በላይ ጎርፍ ሊከሰት እንደሚችል ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን፣ በኢትዮጵያ የተከሰተው የነዳጅ ዕጥረት እንዲሁም የድሬደዋ ስታድየም - የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ከሳኦቶሜ እና ፕሪንስፔ ጋር የሚያደርገውን የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ እንዲያስተናግድ መወሰኑ" የተሰኙትን ጉዳዮች ያስቃኘናል
No matches for "" in this podcast's transcripts.
No topics indexed yet for this podcast.
Loading reviews...
ABOUT THIS SHOW
በዐበይት የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓ እና የዓለም ጉዳዮች ላይ ዜናዎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና ጥልቅ ትንታኔዎች ይቀርባሉ። በዐበይት የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓ እና የዓለም ጉዳዮች ላይ ዜናዎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና ጥልቅ ትንታኔዎች ይቀርባሉ። ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙ የዶይቼ ቬለ ዘጋቢዎች የሚያጠናቅሩት ዜና መፅሔት ከሰኞ እስከ አርብ ከዓለም ዜና ቀጥሎ ይቀርባል። የዶይቼ ቬለን ሥርጭት በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በቀጥታ ማድመጥ ይቻላል። በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ የዶይቼ ቬለን ዜና መጽሔቶች ያዳምጡ።
HOSTED BY
DW
Loading similar podcasts...