PODCAST · news
ዜና መጽሔት
by DW
በዐበይት የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓ እና የዓለም ጉዳዮች ላይ ዜናዎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና ጥልቅ ትንታኔዎች ይቀርባሉ። በዐበይት የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓ እና የዓለም ጉዳዮች ላይ ዜናዎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና ጥልቅ ትንታኔዎች ይቀርባሉ። ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙ የዶይቼ ቬለ ዘጋቢዎች የሚያጠናቅሩት ዜና መፅሔት ከሰኞ እስከ አርብ ከዓለም ዜና ቀጥሎ ይቀርባል። የዶይቼ ቬለን ሥርጭት በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በቀጥታ ማድመጥ ይቻላል። በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ የዶይቼ ቬለን ዜና መጽሔቶች ያዳምጡ።
-
100
DW Amharic የሰኔ 29 ቀን 2018 ዜና መጽሔት
በአፍሪቃ ቀንድ እየጨመረ የመጣው የጦርነት ስጋት፣ የፀጥታ ሥጋት ያጋጠመው የጋሞ ዞን ዛይሴ አካባቢ፣ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ያልተቀመጠዉ የትግራይ ክልል ቅሬታ
-
99
የሰኔ 26 ቀን 2018 የዜና መጽሔት
እቅዱን አሳክቷል የተባለው የኢትዮጵያ የቡና ገቢ ፣ በአሜሪካ የትግራይ ማኅበረሰብ አባላት፣ስለትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ የሰጡት አስተያየት ፣በድሬደዋ የተማሪ ህፃናት ምገባን በተደራጃ መንገድ ማከናወን ያስችላል የተባለ ፕሮጀክት በይፋ መጀመሩ እንዲሁም የቀድሞ የኢራን ላዕላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሚኒ አስከሬን ሽኝት የተሰኙት ርዕሶች ይተነተናሉ።
-
98
የሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
የዜና መጽሔት ዝግጅታችን ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን ታጣቂዎች 13 ሰዎች መግደላቸዉን የሚቃኝ ዘገባ ያስቀድማል።ዜና መፅሔቱ፣ ደቡብ ኢትዮጵያ የኮሬ ዞን አስተማሪዎች ተማሪዎችን ላለመፈተን ማደማቸዉን ከዞኑ አስተዳደር መልስ ጋር ያሰባጠረ ዘገባም አለዉ።የአዉሮጳ የሙቀት መጠን ማየልና የፖለቲካዊ መርሕ ለዉጥ ጥያቄ፣ የቻይና ኮሚንስት ፓርቲ 105ኛ ዓመት በአል፣ የዓለም የእግር ኳስ ግጥሚያ የአፍሪቃ ቡድናት ሽንፈት ያልናቸዉንም ርዕሶች ያስተነትናል።
-
97
የሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
የዜና መጽሔት፤ አዲሱ የመኖሪያ ቤት የኪራይ ዋጋ ጥናት፤ በጋምቤላ ክልል ባህላዊ የግጭት አፈታት ዜዴዎች ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ስለሚኖራቸው ሚና፤ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና መጀመሩ እንዲሁም የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እዚያ ስለሚወለዱ ልጆች ዜግነት ያሳለፈው ውሳኔን የሚያስቃኙ ዘገባዎችን አካቷል።
-
96
የሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
የዜና መጽሔት ዝግጅታችን የኤርትራ የወደፊት ኅልዉና የፕሬዝደንቷ አገዛዝ ያልነዉን ርዕሥ ያስቀድማል። ዜና መፅሔቱ አዲስ አበባ ዉስጥ በተዘዋዋሪ አዉቶብሶች የዲጅታል የሕዝብ አገልግሎት መሰጠቱ፣ የደቡብ አፍሪቃ መጤ ጠል ቡድናት በከፈቱት ዘመቻ ላይ ሊነጋገር የነበረዉ የአፍሪቃ ሕብረት ስብሰባ መራዘምና የዓለም እግር ኳስ ዋንጫን የሚቃኙ ዘገቦችና ቃለ ምልልስን አካቷል።
-
95
DW Amharic የሰኔ 22 ቀን 2018 ዜና መጽሔት
የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድ የኢትዮጵያ ጉብኝት፣ በትግራይ የወጣቶች አፈሳ ቀጥሏል መባሉና የአውሮፓ ህብረት ማስጠንቀቂያ፣ የቀነ ገደቡ መጠናቀቅ እና የፍልሰተኞች ሥጋት በደቡብ አፍሪካ
-
94
የዓርብ ሰኔ 19 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ዜና መጽሔት
ዜናዉን የሚለጥቀዉ የዜና መፅሔት ዝግጅታችን ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አዲስ የደነገገዉን ሕግ እንዲሽር ሑማን ራይትስ ዋች ያቀረበዉን ጥያቄ ህወሃት ዉድማድረጉን የሚተነትነዉን ዘገባ ያስቀድማል።ዜና መፅሔቱ፣ የጋቤላ ብልፅግና ፓርቲ ፅሕፈት ቤት ከተቃዋሚዎች ጋር ተባብሮ ለመሥራት ቃል መግባቱ፣ ደቡብ አፍሪቃ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ጥቃት ይደርስብናል የሚለዉ ሥጋታቸዉ መናሩ፣ የመረጃ ጥቅም፣ የአፍሪቃ አቅምና ዝግጅት፣ እንዲሁም የዓለም የእግር ኳስ የዋንጫ ግጥሚያን የሚቃኙ ዘገቦችና አጭር ዉይይቶች አሉት።
-
93
የሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ለምክክር ጉባኤ የመረጣቸው ስምንቱ አጀንዳዎች፤ በአስተያየት ሰጪዎች ተስፋ እና ሥጋት የተንጸባረቀበት አገራዊ ምክክር፤ የኦሮሚያ ክልሉ ግጭት እና ዘላቂ መፍትሄው፤ የኢቦላ ስርጭትን ለመከላከል የጉዞ እገዳ አስፈላጊ አይደለም ሲል ዐአፍሪካ ሲዲሲ ዐሳወቀ፤ በስፔን ከ200 በላይ ሰዎችን የገደለው የሙቀት ወጀብ በፈረንሣይስ ምን አደረሰ?
-
92
የሰኔ 17 ቀን 2018 የዜና መፅሔት
በዛሬው የዜና መፅሔታችን 4 ርዕሰጉዳዮች ይደመጣሉ። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምሥራቅ ጉራጌ ዞን ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት ሦስት የፀጥታ አባላት መገደላቸውን፤ የትግራይ ጊዚያዊ መስተዳደር ያረቀቀው አስገዳጅ ወታደራዊ ምልመልን እንዲሰርዝ ሂዩማን ራይትስ ዎች መጠየቁን ከተመራጬ መንግስት ምን ይጠበቃል? በሚል መራጮች የሰጡት አስተያየት እንዲሁም የ12 ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን የሚመለከቱ ናቸው በዚሁ ቅደም ተከተል ይደመጣሉ።
-
91
የሰኔ 16 ቀን 2018 የዜና መጽሔት
የዜና መፅሔት ዝግጅታችን ኢትዮጵያ ዉስጥ የተደረገዉን ምርጫ ዉጤት በተመለከተ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሰጡት፣ ድጋፍ፣ ተቃዉሞና ምክርን በሁለት ዘገቦች እንቃኛለን።ከምርጫ ጋር የተያያዘ ነዉ በተባለ ጥራሬ አንድ የቀድሞ ዕጩ መታሰራቸዉን የሚያወሳ ዘገባም ሌላዉ ምርጫነክ ዘገባችን ነዉ።ዜና መፅሔቱ የህወሓት ታጣቂዎች አፋር ክልልን ማጥቃት ሰዎች መግደልና ማቁሰላቸዉንና የማሕበራዊ መገናኛ ዘዴዎች የሚሰራጩ የጥላቻ ንግግሮችን መዘዝ የሚቃኝ ዘገባም አለዉ።
-
90
የሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ/ም የዜና መፅሔት
መጽሄተ ዜናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ትናንት እሁድ ይፋ ባደረገው 7ኛ ው ጠቅላላ ሃገራዊ የምርጫ ዉጤት ላይ ያተኩራል። በቅርቡ ከኢትዮጵያ የተባረረችው ፈረሳያዊቷ ጋዜጠኛን አስመልክቶ ቀጣሪዋ ላክሮዋ ጋዜጣ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ያቀረበው ወቀሳም በዝርዝር ከሚደመጡ ዘገባዎቻችን አንዱ ነው።
-
89
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተጨማሪ ውጤቶችን ይፋ አደረገ
ምርጫ ቦርድ ትናንት ዓርብ ማምሻውን በሰጠው መግለጫ ተጨማሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልል ምክር ቤቶች እጩ አሸናፊዎችን ይፋ አድርጓል፡፡ቦርዱ ይፋ ካደረጋቸው ውጤቶች መካከል የአብን ሊቀመንበር ዶ/ር በለጠ ሞላ እንዲሁም የቀድሞ የባህልና ስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ቀጄላ መርዳሳ በግላቸው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወንበር አሸንፈዋል።
-
88
DW Amharic የሰኔ 12 ቀን 2018 የዜና መጽሔት
በሰኔ 12 ቀን 2018 የዜና መጽሔት የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ “አክራሪ” ባሏቸው የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አባላትና በቤተሰቦቻቸው ላይ የጣሉትን የቪዛ ገደብ የተመለከቱ ሁለት ዘገባዎች ተካተዋል። የውክልና መቀመጫ ያገኙ ፓርቲዎች ቀጣይ መንገድ፣ ሥመ-ጥሩው የሙዚቃ ባለሙያ አዲስ ገሠሠ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፣ ኢትዮጵያ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ሰበብ ከአሜሪካ የሚመጣውን ጫና እንዴት ልትይዝ ይገባል? የሚሉ ዘገባዎችም ይቀርባሉ።
-
87
የሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
የዜና መጽሔት ዝግጅታችን ኢትዮጵያን ወደ ባሕር በር መመለስ በአፍሪካ ቀንድ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና የደህንነት ትብብርን ያጠናክራል መባሉ፤ የተቃዋሚ ፓርቲ እጩዎች ቁጥር ሻል ብሎ የታየበት የምርጫ ውጤት፤ መሶብ» የሚል መጠሪያ የተሰጠው የአንድ ማዕከል አገልግሎት፤ በጥብቅ የመንግሥት ቁጥጥር የሚመራው የቤት ኪራይና ዳራው፤ እንዲሁም የክረምት ወራት የአየር ጠባይ ሁኔታ ትንበያን የሚያስቃኙ ዘገባዎችን አካቷል።
-
86
የሰኔ 10 ቀን 2018 የዜና መጽሔት
አሳሳቢው የጦርነት ስጋት በሰሜን ኢትዮጵያ ፣የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ «የቁጫ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ»ን አቤቱታ ውድቅ ማድረጉ፣ ዩናይትድ ስቴትሰና ኢራን ደረሱበት የተባለው ስምምነት አፍሪካን እንዳያዘናጋ ተንታኛች ማሳሰባቸው እንዲሁም ትራምፕን ጨምሮ የቡድን ሰባት አባል ሀገራት መሪዎች ዩክሬንን ለመደገፍ መስማማታቸው የዛሬው የዜና መጽሔት ዝግጅታችን የሚያተኩርባቸው ጉዳዮች ናቸው
-
85
የጋዜጠኛ ሳልሳዊት ባይነሳኝ እስር
ጋዜጠኛ ሳልሳዊት ባይነሳኝ ከሳምንት በፊት በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሏን ቤተሰቦቿ ለዶቼ ቬለ ገልፀዋል።የጋዜጠኛዋ ታናሽ እህት ለዶይቸ ቬለ እንደገለፀችው፤ እህቷ ያለፈው ሰኞ ሰኔ አንድ ቀን፣ 2018 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ አዲስ አበባ ከሚገኘው መኖሪያ ቤቷ በፖሊስ ለጥያቄ ትፈለጊያለሽ ተብላ ነው የተያዘችው። ያም ሆኖ እስካሁን ፍርድ ቤት አልቀረበችም።
-
84
የሰኔ 9ቀን 2018 የዜና መፅሔት
የዜና መፅሔት ዝግጅታችን ኢትዮጵያ ዉስጥ የኑሮ ዉድነት በደሞዝተኞች ላይ ያሳረፈዉን ጫና ችግር የሚቃኘዉን ዘገባ ያስቀድማል።በትግራይ ክልል አዲስ የወጣዉ የወታደራዊ አገልግሎት ሕግ ያስከተለዉ ተቃዉሞና ሥጋት፣ ኢትዮጵያዊት ጋዜጠኛ መታሰሯና የአፍሪቃ ሕብረት ደቡብ አፍሪቃ ዉስጥ በተቀጣጠለዉ የዉጪ ጠል ጥቃትና ዛቻ ላይ ሊነጋገር ማቀዱን ዜና መፅሔቱ በየተራ ይተነትናል።
-
83
DW Amharic የሰኔ 08 ቀን 2018 የዜና መጽሔት
በሰኔ 08 ቀን 2018 የዜና መጽሔት የቱለማ አባገዳ ሥልጣን ሽግግር እና የቀጣዩ አባገዳ ፈተና፣ የኢራን አሜሪካ ስምምነት እንዲሁም የጡት ወተት ባንክ ምንድን ነው? የሚሉ ርዕሰ-ጉዳዮች ተካተዋል።
-
82
የሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ ጥሪ ነዋሪዎች ከአሸናፊው ፓርቲ ምን ይጠብቃሉ ? ሳዑዲ አረቢያ 4 ኢትዮጵያውያንን በሞት ቀጣች፤ 1655 ዜጎች ደግሞ በምህረት እንዲለቀቁ ተደረገ ለአሜሪካዉያን የኤቦላ ማገገምያ ማዕከል ኬንያ ዉስጥ መገንባቱ ያስነሳዉ ተቃዉሞ እንዲሁም የአውሮፓ ህብረትና ደቡብ ኮሪያ፤ የሰሜን ኮሪይና ቻይና ጉባኤዎች
-
81
የሐሙስ ሰኔ 4 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ዜና መጽሔት
በዜና መፅሔት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ውጤቶችና እያሳወቀ እና ቅሬታዎችንም እያጣራ መሆኑን መናገሩ፣ ሰቆጣ የተጠለሉ የዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ጻግምጅ እና አበርገሌ ወረዳዎች ተፈናቃዮች ለረሀብ መጋለጣቸውን መግለፃቸው ፣ -ደቡብ አፍሪቃ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ሰቆቃ መቀጠሉ ፣ የኤቦላ ስርጭትን ለመከላከል የሚያስችሉ የቅኝት ስራዎች እንዲጠናከሩ መጠየቁ ፣ ዛሬ በሜክሲኮ የሚጀመረው የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ የዜና መጽሔት ዝግጅታችን የሚያስቃኘን ጉዳዮች ናቸው ። በባህል መድረክ ለህክምና ወደ በጀርመን በመጣበት አጋጣሚ እና የስዕል እግዚቢሽን ያቀረበውን ሰዓሊ ብሩክ የሺጥላን እንግዳዉ አድርጓል።
-
80
የሰኔ 3 ቀን፣ 2018 የዜና መፅሔት
ዜናውን የሚከተለው የዜና መጽሔት፣ ጋምቤላ ክልል ዳግም ያገረሸው የፀጥታ ስጋት፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ24 የምርጫ ጣቢያዎችን ውጤት ይፋ ማድረግ መጀመሩ፤ ለመጪው ዓመት ከ2,3 ትሪሊየን በላይ ብር የመንግሥት በጀት መታቀዱ እንዲሁም የዲጂታል ገቢ እና አዲሱ ፈተና የሚያስቃኙ ዘገባዎችን አካቷል።
-
79
የዜና መጽሔት፤ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ማክሰኞ
የዜና መፅሔት ዝግጅታችን የኢትዮጵያ ፈደ,ራዊ መንግሥትና በህወሓት መካከል የናረዉን ዉጥረት ለማርገብ የአፍሪቃ ሕብረትን ሚና የሚቃኝ ቀለ ምልልስን ያስቀድማል።የትግራይ ወጣቶች በብዛት ከክክልሉ መዉጣታቸዉንና ምክንያቱን የሚቃኝ ዘገባም አለዉ።የትራፊክ አደጋ መደጋገምና መፍትሔዉ ሌላዉ የዜና መፅሔት ርዕሳችን ነዉ።ዜና መፅሔቱ የኤርትራና የግብፅ ወዳጅነት ለአፍሪቃ ቀንድ ሰላም የሚኖረዉን በጎ መጥፎ ዉጤት በሚቃኘዉ ዘገባ ያሳርጋል።
-
78
የሰኞ ሰኔ አንድ ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
በዛሬው የዜና መጽሔት ዝግጅታችን አሳሳቢ እየሆነ የመጣዉ የሰሜን ኢትዮጵያ የጦርነት ስጋት በትግራይ የየደረሰዉ የድሮን ጥቃት እና አካባቢዉ ላይ የሚንቀሳቀሱት ታጣቂዎች በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ድምፅ ያልሰጡ በሰሜንና ደቡብ ወሎ መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች፣ ነገ ሰኔ 2 ቀን የምርቻ ድምፅ ሊሰጡ መሆኑ ፤ እንዲሁም ኢሰመኮ - አርሲ ዞን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ምዕመናን እና ቤተክርስትያን ላይ የተፈፀመ ጥቃትን በተመለከተ ክትትል እና ምርመራ እያደረገ መሆኑን መግለፁ በሚሉ ርዕሶች የተቀናበሩት በስፋት ይተነተናሉ።
-
77
-
76
የግንቦት 27 ቀን 2018፤ የዜና መፅሄት
በዜና መጽሔት በአርሲ ዞን የተገደሉ ወገኖችን በሚመለከት የመንግሥት እና መንግሥት ሸኔ የሚለው ታጣቂ ቡድን ምላሽ፤በአማራ ክልል ዋግህምራ ብሔራዊ አስተዳደር የጻግብጂ ወረዳ በአገው ሸንጎ ታጣቂዎች ቁጥጥር ስር ገብቷል መባሉ፤ግንቦት 24 ቀን ስለተካሄደው ምርጫ የተቃዋሚ ፓርቲዎች አስተያየት፤ ድኅረ ምርጫ በደቡብ ሕዝቦች ክልል ፤ በሰባተኛው ምርጫ የተሳተፈው ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ድሬደዋ በሁለት የምርጫ ጣቢያዎች ችግር ደርሶብኛል ማለቱ፤ የዓለም የገንዘብ ድርጅት IMF ለኢትዮጵያ 468 ሚሊየን ዶላር ለመልቀቅ መስማማቱን የሚያስቃኙ ዘገባዎች ተካተዋል።
-
75
የግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
ከምርጫ ማግሥት ማን ምን አለ? የተሰጡ አስተያየቶች፤ በአርሲ የተፈጸመው ግድያ እና የቀረበው አቤቱታ፤ የአፍሪቃ ሕብረት፣ የኢጋድና የኅብረት-ለምርጫ የመጀሪያ ጊዜ ዘገባ፣ የአማራ ክልል ወጣቶች ጥሪ ከምርጫው ማግስት በኋላ፤ ብርን ያዳከመው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሰኞው ምርጫ ላይ ተጽዕኖ ይኖረዋል? ይሰኛሉ ዘገባዎቹ ። ድህረ ምርጫ በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ክልል ቃለ መጠይቅ
-
74
ልዩ ዝግጅት፤ ግንቦት 25 ቀን 2018 ማክሰኞ
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ማግስት ዛሬ በየአካባቢው የወጡ ጊዜያዊ ውጤቶችን እንዲሁም የምርጫውን ሂደት፣ የፀጥታ ችግሮችና እና ተያያዥ ክስተቶችን የሚቃኙ ዘገባዎችን ያካተተ ልዩ ዝግጅት ይዘን ቀርበናል። በምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተነፈገው በዶክተር ደብረፅዮን የሚመራው ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ትናንት የካቢኔ አባላት እና የዞን አስተዳዳሪዎችን ጨምሮ ሌሎች ሹመቶችንም ማጽደቁን መነሻ ያደረገ ዘገባም አለን።
-
73
በምርጫ ከሚያሸንፈው አዲስ አመራር ምን ይጠበቃል?
ትናንት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ/ም ኢትዮጵያውያን በመጭው አመስት አመታት የሚያስተዳድራቸውን ለመምረጥ ድምፅ ሲሰጡ ውለዋል። ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች በተመዘገቡበት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አሸናፊው አካል በቀጣይ አምስት አመታት ሀገሪቱን የማስተዳደር ሀላፊነት ይጣልበታል።ለመሆኑ ከመጭው አዲስ አመራር ምን ይጠበቃል?
-
72
የግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
አርዕስተ ዜና ሰባተኛው ዙር የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ መራጮች ዛሬ ለፌደራል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለክልል ምክር ቤት ለሚወዳደሩ እጩዎች ድምጽ ሲሰጡ ውለዋል። የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኦሮሚያ ክልል በበሻሻ ከተማ የኢትዮጵያ ርዕሰ ብሔር ታዬ ዐፅቀ ሥላሴ ደግሞ በአዲስ አበባ ዛሬ ጠዋት ድምጽ ሰጥተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ “በጸጥታ ምክንያት ወደ 143 የሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች ” አለመከፈታቸውን ዛሬ አስታወቀ። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላተ ወርቅ ኃይሉ በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ የተወሰኑ የምርጫ ክልሎች የድምጽ አሰጣጥ ከተጀመረ በኋላ በጸጥታ ችግር መቋረጡን ተናግረዋል።
-
71
የግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጎሀፅዮን አካባቢ፤ ከአዲስ አበባ ወደ አማራ ክልል የጓሚዙ 12 መንገደኞች መገደላቸውን መጭው ምርጫ ከተሳታፊ ፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ከታዛቢዎች እና ከመራጮች አንፃር በአማራ ክልል አሽከርካሪዎች በክልሉ ባለው ግጭት ሳቢያ ግድያ እና ዝርፊያ እየደረሰብን ነው ማለታቸው በደቡብ አፍሪቃ የሚታየውን የመጤ ጠል ጥቃት የሚያስቃኙ አራት ዘገባዎችን አካቷል።
-
70
DW Amharic የግንቦት 20 ቀን 2018 የዜና መጽሔት
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ማስጠንቀቂያና የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምላሽ፣ የሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ድባብ በአዲስ አበባ፣ ''ምርጫው፣ አገሪቱን ወደ ባሰ ቀውስ ሊያሸጋግር የሚችል ነው።''የጋራ-መድረክ፣ ምርጫና የሴቶች ተሳትፎ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣
-
69
የረቡዕ ግንቦት 19 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ዜና መጽሔት
የዓለም ዜናን የሚከተለው የዜና መጽሔት፤ አዲስ አበባን ጨምሮ ከተለያዩ አካባቢዎች የደረሱንን የኢድ አል አድሀን በዓል የተመለከቱ ዘገባዎች ያስቀድማል፤ የመጨረሻው የምርጫ ቅስቀሳ እና የፓርቲዎች አስተያየት፤ እንዲሁም የአፍሪቃ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን አዲስ አበባ መግባቱን የሚያስቃኙ ዘገባዎችን አካቷል። በትግራይ ክልል “የወጣቶች የግዳጅ ምልመላ” እየተደረገ መሆኑ መገለጹ፤ በተጨማሪም የትግራይ ክልልን ወቅታዊ ሁኔታ በሚመለከት ከህወሃት ቃል አቀባይ ጋር አጭር ቃለ ምልልስ አድርገናል።
-
68
የግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
በዜና መጽሔት አምስት ዘገባዎችን እናስተነትናለን ። በአማራ 8፣ በትግራይ 38 ምርጫ ክልሎች ላይ ግንቦት 24 ምርጫ አይደረግም መባሉ፤ የተፎካካሪ ፓርቲዎች የምርጫ ቅስቀሳ በአማራ ክልል፤ የምርጫ ቅስቀሳቃ እና ፖለቲካ ፓርቲዎች አስተያየት፤ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የምርጫ ዘመቻ እንዲሁም የአፍሪቃ ኅብረት ባልተጠናቀቁ የቤት ስራዎቹ ላይ ማተኮር እንዳለበት ተገለፀ በሚሉ ርዕሶች ስር ተጠናቅረዋል።
-
67
የግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
በፓርቲው ምክትል ሊቀ መንበር የሚመራው የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ ክፋይ ምርጫ ቦርድ "የዜጎችን መሠረታዊ የሰብአዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ሊነጥቅ አይገባም" ሲል ማሳሰቡን፤ የጎጎት ለጉራጌ አንድነት እና ፍትህ ፓርቲ በምርጫ ቅስቀሳ ላይ " ስልታዊ የሆኑ የምርጫ ሕግ ጥሰቶች ካልታረሙ ከምርጫው እራሱን ለማግለል እንደሚገደድ ማሳወቁን፤ በትግራይ ስላለው የጦርነት ድባብ የባለሙያ አስተያየት
-
66
የዜና መጽሔት፤ ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም
የዜና መጽሔት-1-በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ዝግጅት- 2-ራሳቸውን ከምርጫ ያገለሉ የድሪዳዋ ከተማ እጩ ተወዳዳሪና ሐረሪ ክልል የሚንቀሳሱ ሌላ እጩ ተወዳዳሪ ስለ ምርጫው ሂደት የሰጡት አስተያየት 3 -የንግድ ሱቆቻቸው የፈረሱባቸው ደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሮሮ-4-ወደ ውጭ የሚላክ የኢትዮጵያ ቡና ላይ የተጋረጠው ፈተና - 5 ቻይና በዓለም ኃያላን ተፈላጊ የሆነችበት ምክንያት በሚሉ ርዕሶች ስር የተቀናበሩ ዘገባዎች ይቀርቡበታል ሳምንታዊው ከወጣቶች ዓለም ከምርጫ 2018፤ ወጣቱ በርግጥ ምን ይፈልጋል?- በሚል ርዕስ ጋር ከተቀናበረ ዝግጅት ጋር ይጠብቀናል ።
-
65
የግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
የዜና መጽሔት፤ ምርጫ ቦርድ ያሰማራው የፀጥታ ኹኔታን የቃኘው ቡድን ያቀረበው ውጤትና የፓርቲዎች አስተያየትን ያስቀድማል፤ በምርጫ 2018 እና የተቀዛቀዘው የኦፌኮ ተሳትፎ፤ የደቡብ ወሎ የምርጫ ካርድ ውዝግብ ታግተው የነበሩ ከመቶ በላይ የፍንጫ ስኳር ፋብሪካ ጊዜያዊ ሠራተኞች መለቀቀቅ፤ የብሔራዊ ባንክ የ500 ሚሊዮን ዶላር ጨረታ እና የኑሮ ውድነት ስጋት እንዲሁም አፍሪካ ሲዲሲ ኢቦላ አስቸኳይ የኅብረተሰብ ጤና አደጋ ነው ማለቱን የሚስቃኙ ስድስት አካቷል።
-
64
የግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
በዜና መጽሔት አራት ዘገባዎችን እናስተነትናለን ። በሰሜን ወሎ ዞን ነዋሪዎች ለቀጣዩ ምርጫ «እንኳን ሌላ ፓርቲ ብልጽግናም ራሱ አይቀሰቅስም» ማለታቸው፤ ጠ/ሚ ዐቢይ ስለ ሥራና ሠራተኛ ባሰሙት ንግግር የሰዎች አስተያየት፤ የሁለት ዓመት አስገዳጁ የቤት ኪራይ ውል አዋጅ ሊያበቃ መቃረቡ፤ እንዲሁም የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲ (ሲፌፓ) በምርጫ ቦርድ ላይ ክስ መመሠረቱ ይሰኛሉ ዘገባዎቹ ።
-
63
-
62
-
61
የግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
ዜና መጽሔት -ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ ኢትዮጵያውያን ላይ የቀጠለው ጥቃት -ስለምርጫ ዝግጅት ከአዲስ አበባ እና ከደሴ የተሰባሰበ የሕዝብ አስተያየት -ፈረንሳይ በአፍሪካ አዲስ አጋሮችን እየፈለገች ነው -የአሜሪካ ፕሬዝደንት የቻይና ጉብኝት እና የሁለቱ ሃገራት ግንኙነት እና አዲስ የኤች አይ ቪ መድኃኒት ወደ ኢትዮጵያ ሊገባ መታቀዱን ያስቃኘናል።
-
60
-
59
የግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
መተከል ዞን ጉባ ወረዳ ከ30 በላይ መንገደኞች በታጣቂዎች መገደላቸዉን የሚያወሳዉን ዘገባ ያስቀድማል።የህወሓት አባላት ናቸዉ የተባሉ ታጣቂዎች ከራያ አለማጣ ከተማ 50 የቤተ-ክሕነት ተማሪዎች ማገታቸዉ ከደሴ ሲዘገብ፣ የኢትዮጵያ የሲቪል ማሕበራት ሕብረት አንዳድ አካባቢ በመራጮች ምዝገባ ሒደት ሕግ መጣሱን አስታዉቋል።ዜና መፅሔቱ የትግራይ ጋዜጠኞች ከክልሉ ወደ ሌላ አካባቢ ለመሔድ መገደዳቸዉን የሚቃኝ ዘገባም አለዉ።
-
58
የግንቦት 4 ቀን 2018 የዜና መፅሔት
የዓለም ዜናውን በሚከተለው የዜና መጽሔት፣-በዋግ ኸምራ ዞን የአበርገሌ ወረዳ ተፈናቃዮች አቤቱታ፤ ዓለም አቀፉ የፍልሰኞች ድርጅት የአፍሪካ ቀንድ ፍልሰተኞች በአደገኛው መስመር መጓዛቸውን አላቆሙም ማለቱ፤ የኢትዮጵያ የምርጫ ስርዓት፤ አብላጫ ድምጽ ወይስ ተመጣጣኝ? ፤ የአውሮፓ ሕብረት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የስብሰባ ትኩረት እንዲሁም ከመሬት ለአራሹ ትግል እስከ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የዘለቁትና ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት አቶ ዘገየ አስፋውንም የሚያስታውስ ጥንቅር አካቷል።
-
57
የግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
በዜና መፅሄት ጥንቅራችን -ለሰባተኛው ዙር ምርጫ የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በገንዘብ ድልድል ላይ ያቀረቡት ቅሬታ -የኢኮኖሚ ዕድገት መመዘኛ የሕዝቡን የኑሮ ሁኔታም ከግምት ማስገባት አለበት መባሉን -የአየር ንብረትን መቋቋም የሚያስችል የግብርና ቴክኖሎጂን የተመለከተ ዓለም አቀፍ ስብሰባ በሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ መካሄዱን -የኢራን የሰላም ዕቅድ በአሜሪካ ውድቅ መሆኑን የተመለከቱ ዘገባዎች ተካተዋል።
-
56
የዓርብ ሚያዝያ 30 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ዜና መጽሔት
ቀዳሚውን የዓለም ዜና በሚከተለው የዜና መጽሔት -የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)የቅድመ ምርጫ ሂደቶች ላይ ጥሰቶች እንደነበሩ መግለጹ ፣በአማራ ክልል በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚሳተፉ ተፎካካሪ ሀገራዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች ስሞታ፣ ስለ መገናኛ ብዙኃን ምኅዳር የመንግሥት፣ የባለሙያዎች እና አጥኚዎች ዕዉነት፣ -የነዋሪዎችን ህይወት ያቃወሰው የትራንስፖርት እጥረት በኢትዮጵያ፣ -የሞት ፍርድን የሚጠባበቁትን ጨምሮ ሰነድ አልባዎቹ ኢትዮጵያዉያን በሳዉዲ፣ የዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን ተኩስ አቁም ወዴት ያመራ ይኾን? በተሰኙ ርዕሶች ስር የተጠናቀሩ ዘገባዎች ይቀርባሉ ሳምንታዊ የወጣቶች ዓለምም በሰዓቱ ይቀርባል።
-
55
የሚያዚያ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
በዜና መጽሔት የደቡብ አፍሪቃው ዘመቻ ዱዱላ’ ኢትዮጵያዉያንን ጨምሮ ሕገ-ወጥ ስደተኞችን እያደነ ነው፤ የወለንጪቲ የልማት ተነሺ ገበሬዎች ካሳ አልተከፈለንም ሲሉ ማማረራቸውን፤ የሙዝ አምራች አርሶ አደሮች የገበያ ተግዳሮት ፤ ዩናይትድ ስቴትስ ለኢትዮጵያ የምትሰጠው ርዳታ እንዳይቋረጥ መጠየቁ እንዲሆም ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ከምትልካቸው ምርቶች 10 ቢልዮን ዶላር ለማግኘት ማቀዷ በሚሉ ርዕሶች ስር የተቀናበሩ ዘገባዎች ይቀርባሉ።
-
54
የሚያዚያ 28 ቀን 2018 ዓ/ም የዜና መጽሔት
አሜሪካ የኤርትራን ማዕቀብ ለማንሳት ማጤኗ ለኢትዮጵያ በረከት ወይስ መዘዝ? ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ ኢትዮጵያውያን በተለየ መንገድ የጥቃት ኢላማ መሆናቸው የአላማጣና አካባቢው ወጣቶች የጦርነት ሥጋትና ስደት የሱዳን ክስና እና የኢትዮጵያ ምላሽ ህወሓት ትናንት የወሰደው 'ርምጃ እና የሚኖረው ውጤት
-
53
የማክሰኞ ሚያዝያ 27 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ዜና መጽሔት
ዛሬ ታስቦ የዋለዉን 85ኛ የኢትዮጵያዉያን የድል በዓል መታስብያን በማስታከክ ፤ የአርበኞች ድል መታሰቢያ እና የዛሬው ትውልድ ለሕብረት ያለው አቋም ሲል የሚያጠይቅ ዘገባን ይዘናል። ለ7ኛዉ ጠቅላላ ምርጫ ቅስቀሳ ተግዳሮት ገጠመን ያሉ ተፎካካሪ ፓርቲዎች በደቡብ ወሎ ዞን እንዲሁም በኢትዮጵያ የነዳጅ ዋጋ ላይ የተደረገው የመሸጫ ዋጋ ጭማሪ እና የሚያሳድረዉ ጫናን የሚዳስስ ዘገቦችም በተከታታይ ይቀርባሉ። የአሜሪካዉ ትራምፕ በጀርመን ከሰፈሩ የአሜሪካን ወታደሮች መካከል ወደ 5,000 የሚሆኑትን ለማስወጣት እቅድ መያዛቸዉ እና የተሰጡ ግብረ መልሶችን የሚዳስስ ዘገባንም ይዘናል።
-
52
-
51
የሚያዝያ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት
የደቡብ አፍሪቃው መጤ ጠል እንቅስቃሴ ኢትዮጵያውያንን ብርቱ ስጋት ላይ ጥሏል አውሮፓ ሕብረት የፕሪቶሪያን ስምምነት አደጋ ላይ የሚጥሉ 'ርምጃዎች እንዲረግቡ ጠየቀ “አገልግሎታችንን ወደ አምስት ኮከብ ማሳደግ እንፈልጋለን” የኢትዮጵያ አየርመንገድ ዓለም አቀፉ የሠራተኞች ቀን በኢትዮጵያ ሲታወስ ወደ ከተሞች የሚደረግ ከፍተኛ ፍልሰት የቤት አቅርቦት ቀውስ ፈጥሯል-ተመድ
We're indexing this podcast's transcripts for the first time — this can take a minute or two. We'll show results as soon as they're ready.
No matches for "" in this podcast's transcripts.
No topics indexed yet for this podcast.
Loading reviews...
ABOUT THIS SHOW
በዐበይት የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓ እና የዓለም ጉዳዮች ላይ ዜናዎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና ጥልቅ ትንታኔዎች ይቀርባሉ። በዐበይት የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓ እና የዓለም ጉዳዮች ላይ ዜናዎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና ጥልቅ ትንታኔዎች ይቀርባሉ። ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙ የዶይቼ ቬለ ዘጋቢዎች የሚያጠናቅሩት ዜና መፅሔት ከሰኞ እስከ አርብ ከዓለም ዜና ቀጥሎ ይቀርባል። የዶይቼ ቬለን ሥርጭት በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በቀጥታ ማድመጥ ይቻላል። በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ የዶይቼ ቬለን ዜና መጽሔቶች ያዳምጡ።
HOSTED BY
DW
Loading similar podcasts...