PODCAST · business
ምጣኔ ኃብት - የአሜሪካ ድምፅ
by VOA
የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) ከአርባ በላይ በሆኑ ቋንቋዎች ከዩናይትድ ስቴትስ በመላው ዓለም የሚያሠራጭ አገልግሎት ነው፡፡ ቪኦኤ በየሣምንቱ ወደ 1 ሺህ 500 ሰዓት ለሚሆን ጊዜ ዜና፣ መረጃዎችን፣ ትምህርታዊና ባሕላዊ ፕሮግራሞችን በዓለም ዙሪያ ወደ 123 ሚሊየን ለሚሆን ሰው ያደርሣል፡፡ የበለጠ ለማወቅ በ voanews.com ላይ ያግኙን፡፡
-
50
-
49
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዕድገት ዕድል ድንጋጌ (አጎአ)አባል ሆና መቀጠል ይኖርባታልን? - ኦክቶበር 28, 2021
በጎረጎሳዊያኑ 2000 ዓመተምህረት የተፈረመው የአፍሪካ ዕድገት ዕድል ድንጋጌ (አጎአ) ዩናትይድ ስቴትስ እና አፍሪካዊያን ሀገራትን በንግድ ዘርፍ ያጣመረ ሰነድ ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጦርነት እና ሰብዓዊ መብቶች ረገጣ ደጋግሞ ስሟ የተነሳው ኢትዮጵያ ከዚህ የተጠቃሚነት ሰነድ ልትሰረዝ እንደምትችል ስጋት አይሏል። ሀብታሙ ስዩም ይሄ እንዳይሆን ዘመቻ ከጀመሩ ፣ በአንጻሩ ደግሞ እርምጃው እንዲወሰድ የሚፈልጉ ትውልደ -ኢትዮጵያዊያንን ሀሳብ በመቀጠል ያሰማናል ።
-
48
-
47
የዋጋ ንረት እና የኑሮ ውድነት በአዲስ አበባ - ኦገስት 31, 2021
የዋጋ እጅግ እያሻቀበ መምጣትና የኑሮው መወደድ የየዕለት ፈተና እየሆነባቸው መሆኑን አስተያየታቸውን ለአሜሪካ ድምፅ የሰጡ የአዲስ አበባ ተናግረዋል። በሀገሪቱ እየታየ ያለው የኑሮ ውድነት መንስዔዎች የኮቭድ 19 ወረርሽኝና ሀገሪቱ የገባችበት ጦርነት መሆናቸውን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህር የሆኑት የምጣኔ ኃብት ባለሙያ ዶክተር ብርሃኑ ደኑ ገልፀዋል። ቀውሱን ለመቆጣጠር መንግሥት የተለያዩ ምጣኔ ኃብታዊ የእርምት እርምጃዎችን እየወሰደ እንደሆነ እየተገለፀ ነው።
-
46
ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞች በቦሳሶ - ጁን 19, 2021
በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን በፑንትላንድ ሶማሌ ቦሳሶ በሚገኘው የዓለም አቀፍ የስደተኞች ተቋም IOM በኩል ለመመለስ መወሰናቸውን ተሰምቷል፡፡የአሜሪካ ድምጽ እነዚህን ወጣቶችና በኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የስደተኞች ተቋም IOM ውስጥ የስደተኞች መልሶ ማቋቋም ብሔራዊ መርሃግብር አባል የሆኑትን እከዳር ጤናዬን አነጋግሯል፡፡
-
45
-
44
-
43
ጥቅሙ ሲያበቃ አትክልት ሆኖ የሚበቅለው ቦርሳ መስራች - ማርች 25, 2021
ረድኤት ታደሰ ተጠቅመው ሲጨርሱት ለም መሬት ላይ አትክልት ሆኖ መብቀል የሚችል የወረቀት ቦርሳ ለገበያ አብቅታለች፡፡ አሁን ላይ 'ፕላንተብል ባግስ' ስትል የሰየመችው የሚበቅል ቦርሳ በትንሽ መጠን ብቻ እየተመረተ ሲሆን ስራውን ለማስፋትም በብሉሙን የስራ ፈጣሪዎች ውድድር ላይ ገብታ ለመጨረሻው ዙር ካለፉት መሃከል ሆናለች፡፡
-
42
-
41
"ወጣቶች ዩኒቨርስቲ ከገቡበት ጊዜ ጀምሮ ስለ ስራ ማሰብ መጀመር አለባቸው" አቶ ኤፍሬም በቀለ - ማርች 11, 2021
ከከፍተኛ የትምህርት እና የሙያ ተቋማት እየተመረቁ የሚወጡ እጅግ ብዙ ወጣቶች በስራ ገበያው ላይ ተመጣጣኝ ስራ ሲያገኙ አይታይም፡፡ በዚም ምክንያት የተማሩ ወጣቶች በስራ ፍለጋ ከወራት እስከ ዓመት ሲጉላሉ ይስተዋላል፡፡ በአንጻሩ ቀጣሪዎችም ተወዳዳሪ የሆኑ ወጣቶች በበቂ ሁኔታ ገበያው ላይ እንደሌሉ ሲያነሱ ይሰማል፡፡ የስነልቦና ባለሞያ እና የስራ ቅጥር አማካሪ የሆኑት አቶ ኤፍሬም በቀለ ወጣቶች ስለ ስራ ማቀድ ያለባቸው ሲመረቁ ሳይሆን ገና ትምህርት ሲጀመሩ ነው ይላሉ፡፡
-
40
ኢትዮጵያ ውስጥ ወጣቶች የስራ ፈጠራ ሃሳባቸውን መሸጥ ይችሉ ይሆን? - ማርች 03, 2021
ኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የተማረ ወጣት ሃይል እየተፈጠረ መሆኑን ተከትሎ ብዙዎች የራሳቸው የስራ ፈጠራ ሃሳብ እያመንጩ ይገኛሉ፡፡ ይሁንና ብዙዎቹ የስራ ፈጠራቸውን ለመሞከርም ሆነ ወደ ተግባር ለማምጣት የመነሻ ወረት እጥረትና በንግድ ክህሎት ማነስ ምክንያት ህልማቸውን ማሳካት ሲያቅታቸው ይታያል፡፡ ይህን በተመለከተ የአይስ አዲስ መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ማርቆስ ለማን ኤደን ገረመው አነጋግራዋለች፡፡
-
39
በኢትዮጵያ የተመረቱ የተፈጥሮ ሽቶዎችን ለገበያ ያበቁት ወጣቶች ጉዞ - ፌብሩወሪ 23, 2021
በኤዶም በቀለ እና ሰናይት ዳንኤል ሉሲ ፍራግራንስ አትዮጵያዊ የሆነ መዓዛ ያለው የሽቶ ማምረቻ ድርጅትን ስራ ካስጀምሩ ሶስት ወራት ተቆጠሩ፡፡ ከዩኒቨርስቲ ከተመረቁ አራት ዓመታት ያስቆጠሩት ሁለቱ ጓደኛሞች ከተፈጥሮ ግብዓቶች የተመረቱ ሃይላንደር እና ኢቮልቭ የተሰኙ የወንድ እና የሴት ሽቶዎችን ለገበያ አብቅተዋል፡፡
-
38
የኢትዮጵያ እዳ፣ ዩሮ ቦንድ እና ቡድን 20 - ፌብሩወሪ 03, 2021
ኢትዮጵያ እኤአ በ2014፣ እንደ ፋይናንስ ምንጭና መበደሪያ ይሆናት ዘንድ የ1 ቢሊዮን ዶላር ቦንድ ሸጣለች፡፡ ለሽያጩም በየዓመቱ ከ62 ሚሊዮን ዶላር በላይ ወለድ ትክፍልበታለች፡፡
-
37
እቁብን ከብዙ ሰዎች ጋር በእጅ ስልክ አማካኝነት መጣል የሚያስችለው መተግበሪያ - ጃንዩወሪ 06, 2021
ዮሃና ኤርሚያስ የ25 ዓመት ወጣት እና የቴክኖሎጂ ባለሞያ ናት፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ በባህላዊ መንገድ ሰዎች ገንዘብ የሚቆጥቡበት እና እቁብን በቀላሉ ለመሰብሰብ እና እና ለመክፈል የሚያግዝ መተገበሪያ ይፋ ለማድረግ ከከአጋሯ ጋር በሙከራ ሂደት ላይ ትገኛለች፡፡
-
36
በአንድ የስደተኛ ጣቢያ ውስጥ ብቻ 158 የሚሆኑ ከወላጆቻቸው ጋር የተጠፋፉ ሕጻናት አሉ - ዲሴምበር 03, 2020
አንድ መቶ ሃምሳ ስምንት የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ሕጻናት ከወላጅ እና ከቅርብ ዘምዶቻቸው ተንጥለው በሱዳን ኡም ራክባ የስደተኞች ጣቢያ ውስጥ ለጥቃት እና ጉልበት ብዝበዛ ተጋላጭ በሆነ ሁኔታ ወስጥ መኖራቸውን ሴፍ ዘ ችልድረን አስታወቀ፡፡ ኤደን ገረመው በሱዳን የሴቭ ዘ ችልድረን ዳይሬክተር አርሻድ ማሊክን አነጋግራ ተከታዩን አሰናድታለች፡፡
-
35
ዩኒቨርስቲዎች ሲከፈቱ ሊከሰቱ የሚችሉ ግጭቶችን ታሳቢ በማድረግ ለግቢ ጥበቃዎች በፌደራል ፖሊስ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ - ኦክቶበር 28, 2020
ለፈው ግማሽ ዓመት ተፈጥረው የነበሩ የተማሪዎች ግጭት እና የትምህርት መስተጓጎል ተሞክሮ በመነሳት እና መጪው የምርጫ ወቅት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከፌዴራል ፖሊስ ጋር በመተባበር ለግቢ ጥበቃ አባላት በዩኒቨርስቲዎች ውስጥ የሚነሱ የብሄር እና የፖለቲካ ግጭቶችን ለመቆጣጠር የሚያስችል ስልጠና በሃገር አቀፍ ደረጃ መስጠት ጀምሯል፡፡
-
34
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዲስ መመሪያ አወጣ - ክፍል ሁለት - ኦክቶበር 13, 2020
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሰሞኑን ባወጣው መመሪያ ለግለሰብ በቀን ማውጣት የሚፈቀደው ከፍተኛው የጥሬ ገንዘብ መጠን ወደ 50,000 ብር ዝቅ እንዲል ወስኗል። ለድርጅቶች የሚፈቀደው ደግሞ በቀን 75, 000 ብር ብቻ መሆኑ በመመሪያው ተመልክቷል።
-
33
-
32
-
31
-
30
"የሕዋ ሳይንስ ትምህርት እና ኢንደስትሪው ትይዩ መገንባት አለባቸው" ትንሳኤ አለማየሁ - ኦክቶበር 11, 2020
ትንሳኤ አለማየሁ የአራተኛ ዓመት የመቀሌ ዩኒቨርስቲ የመካኒካል ምህንድስና ተማሪ፤ በመቀሌ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ ህዋ ሳይንስ ማኅብረሰብ ምክትል ሊቀመንበር እና በተባበሩት መንግስታት የስፔስ ጄኔሬሽን አማካሪ ቢሮ የኢትዮጵያ ተጠሪ ነው፡፡ ከሰሞኑም ሃገሩን ወክሎ የአፍሪካ ወጣቶች በህዋስ ሳይንሱ በሰፊው እንዲሳተፉ ምን መደረግ እንዳለበት ረቂቅ ጽሁፍ የህዋ ጠበብት በሚያዘጋጀው ስብሰባ ላይ ሊያካፍል ዝግጅቱን ጨርሷል፡፡
-
29
"ወደ ውድድሮች የገባሁት ለስራ ማስኬጃ ገንዘብ ስላስፈለገኝ ነው" የፈጠራ ባለሞያ ቃለዳዊት - ሴፕቴምበር 05, 2020
ቃለዳዊት እስመለዓለም በባህርዳር ከተማ የሚኖር ወጣት የኮምፒውተር ሳይንስ መምህር እና የፈጠራ ባለሞያ ነው፡፡ ከቃለዳዊት ፈጠራ ስራዎች መሃከል በዋናነት የሚነሱት የዶሮ እንቁላል ማስፈልፈያ ኢንኩቤተር፤ የትራፊክ መብራት እና ሙሉ ለሙሉ በሃገር ውስጥ የተመረተ የጸሃይ ሃይል መሰብስቢያ ሶላር ናቸው፡፡ ቃለዳዊት በተለያዩ ውድድሮች ላይ በመሳተፍ ሽልማቶችን አግኝቷል፡፡ በውድድሮቹ ላይ የሚሳተፈውም ያለበትን የበጀት እጥረት ለሟሟላት እንደሆነ ይናገራል፡፡
-
28
ኢትዮጵያዊቷ እድሜያቸው ከ30 በታች ሆነው በአፍሪካ ሕዋ ላይ ተጽዕኖ እየፈጠሩ ያሉ ምርጥ 10 ዝርዝር ውስጥ ገባች - ሴፕቴምበር 03, 2020
ሊዲያ ረዘነ በቱርክ እና በቻይና የሕዋ ምሕንድስና እንዲሁም በማላዊ የቴክኖሎጂ ማዕከል ውስጥ የሰው አልባ በራሪ ድሮን መግጠም ስልጠና ለ 3 ወራት ወስዳለች:: በቅርቡም የአፍሪካን የሕዋ ሳይንስ መረጃ መተንተኛ ድረ ገጽ እድሜያቸው ከ 30 ዓመት በታች የሆኑ እና በአፍሪካ ሕዋ ላይ ተጽእኖ እያሳደሩ ካሉ ምርጥ አስሮች ውስጥ አካቷታል፡፡ ኤደን ገረመው ተከታዩን አሰናድታለች፡፡
-
27
ኢትዮጵያ በመጪው ጥቅምት ሁለተኛ ሳተላይት ልታመጥቅ ነው፡፡ - ኦገስት 25, 2020
ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት ጥቂት ወራት ውስጥ ከቻይና ጋር በመተባበር ሁለተኛ ሳተላይት ወደ ህዋ ለማመንጠቅ ዝግጅቷን እያጠናቀቀች መሆኑን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ቲክኖሎጂ ኢኒስቲቲዩት አስታወቀ፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ኤደን ገረመው የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሰለሞን በላይ አነጋገራ ተከታዩን ዘገባ አሰናድታለች፡፡
-
26
የኢትዮጵያ የማዕድን እና የነዳጅ ሀብት እምቅ አቅም - ኦገስት 24, 2020
የኢትዮጵያ የማዕድን እና የነዳጅ ሀብት እምቅ አቅም በተነገረበት መድረክ ላይ የሃገሪቱ የማዕድን እና ነዳጅ ዘርፍ ፖሊሲ እየተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
-
25
በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከምዝገባ እስከ ምረቃ ድረስ በድረገጽ ትምህርት መስጠት የሚያስችላቸው አሰራር ይፋ ሆነ፡፡ - ኦገስት 05, 2020
በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሙሉ ጊዜ የድረገጽ (ኦን ላይን) ትምህርት ማካሄድ እንዲችሉ የሚፈቅድ መመሪያ በከፍተኛ የትምህርት አግባብነት ጥራት ኤጀንሲ እና በሳይንስ እና በከፈተኛ ትምህርት ሚኒስተር በዛሬው ዕለት ይፋ አድርገዋል፡፡በዚህ ጉዳይ ላይ ኤደን ገረመው በከፍተኛ ትምህርት አግባብነት እና ጥራት ኤጀንሲ የእውቅና አሰጣጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አብይ ዲባይን ያደረገችው ቆይታ እንደሚከተለው ይሰማል፡፡
-
24
ኢትዮጵያዊው የሃርማን ጄምነርን ሽልማት አሸነፈ - ኦገስት 01, 2020
በኤስ ኦ ኤስ ማሳደጊያ ውስጥ ያደገው ኢትዮጵያዊው ገብረእግዚአብሄር ገብረ በዛሬው ዕለት የሃርማን ጄምነር ሽልማት አሸናፊ መሆኑ ይፋ ተደርጓል፡፡ገብረእግዚአብሄር ለውድድር የቀረበው በልኡል ግርማይ መታሰቢያ ድርጅት በኩል ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የአፍሪካ ሃገራት ለሚያደርገው የትምህርት ድጋፍ ነው፡፡ ኤደን ገረመው ገ/እግዚአብሔርን እና የኤስ ኦ ኤስ እናቱን ወ/ሮ መድህን መሃሪን አነጋግራለች፡፡
-
23
በአሁኑ ሰዓት ከ10 ሺ በላይ ሰዎች የእኛን ሰብዓዊ ድጋፍ ይሻሉ - ያሬድ ሹመቴ - ጁላይ 25, 2020
ባለፉት ሳምንታት በነብሩ ሁከቶች ሳቢያ ብዙዎች ከመኖሪያ ቤት ተፈናቅለው ንብረታቸውንም በማጣት አስቸኳይ የሰብዓዊ ድጋፍን ይሻሉ፡፡ ጥምረት ለሰብዓዊ ድጋፍ በሃገር ፍቅር ትያትር ቤት ግቢ ውስጥ በመገኘት የቁሳቁስ ድጋፎችን ለማሰባሰብ ጥሪ አድርጓል፡፡
-
22
በአዲስ አበባ ከ65,000 በላይ መምህራን የሚሳተፉበት የክረምት ጥናት መርሃግብር ተጀመረ - ጁላይ 25, 2020
የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ በኮቪድ 19 ሳቢያ ትምህርት አቋርጠው የተቀመጡ የአንደኛ እና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችን ለማገዝ 65,000 የሚሆኑ በጎፍቃድኛ መምህራንን አስተባብሮ 'ት/ቤቴ በቤቴ' የሚል የክረምት የጥናት መርሃግብር መጀመሩን አስታውቋል፡፡
-
21
በኢትዮጵያ የድንገተኛ አደጋዎች ቅድመ ማስጠንቀቂያ አገልግሎት ሊጀመር ነው - ጁላይ 16, 2020
የኢትዮጵያ የሰላም በሰው ሰራሽ እና ተፈጥሮአዊ በሆነ መልኩ ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎችን ቀድሞ ለኅብረተሰቡ ለማሳወቅ የሚያስችል የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓት ዝርጋታ እየጨረስኩ ነው ሲል አስታውቋል፡፡ ማስጠንቀቂያ ሲኖር በስልክ እንድሚላክ ተገልጿል፡፡
We're indexing this podcast's transcripts for the first time — this can take a minute or two. We'll show results as soon as they're ready.
No matches for "" in this podcast's transcripts.
No topics indexed yet for this podcast.
Loading reviews...
ABOUT THIS SHOW
የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) ከአርባ በላይ በሆኑ ቋንቋዎች ከዩናይትድ ስቴትስ በመላው ዓለም የሚያሠራጭ አገልግሎት ነው፡፡ ቪኦኤ በየሣምንቱ ወደ 1 ሺህ 500 ሰዓት ለሚሆን ጊዜ ዜና፣ መረጃዎችን፣ ትምህርታዊና ባሕላዊ ፕሮግራሞችን በዓለም ዙሪያ ወደ 123 ሚሊየን ለሚሆን ሰው ያደርሣል፡፡ የበለጠ ለማወቅ በ voanews.com ላይ ያግኙን፡፡
HOSTED BY
VOA
CATEGORIES
Loading similar podcasts...